Monday, May 19, 2014

ከዞን-9 ታሣሪዎች ስድስቱ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ፖሊስ በሽብር አድራጎት እጠረጥራቸዋለሁ ብሏል፤ ፍርድ ቤት የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የፊደል ቁመት 
መለስካቸው አምሃ
 —   
የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/

ላለፉት 23 ቀናት ክሥ ሳይመሠረትባቸው ታስረው ከሚገኙት ዘጠኝ የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ሚድያ ፀሐፊዎች የሆኑ ጋዜጠኞችና አምደኞች ስድስቱ ዛሬ፤ ቅዳሜ፣ ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት የጋዜጠኞቹንና የአምደኞቹን ጉዳይ ያየው በዝግ ሲሆን የቀረቡት ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋዓለም ወልደየስ እና ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ሌሎች ሦስት አምደኞች መሆናቸው ታውቋል፡፡
  
የዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡየዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡ
ዛሬ ችሎት ያልቀረቡት አምደኞች መቼ እንደሚቀርቡ ለጊዜው በትክክል ባይታወቅም ሰሞኑን ይቀርባሉ የሚል ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡

Thursday, May 15, 2014

እምዬ ምኒልክ ሲመጥቅ፣ ወያኔ ሲወድቅ


May 15, 2014
ከሮበሌ አባቢያ፤ 14/5/2014
ቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ
ወያኔ በ1983 አዲስ አበባ ሲገባ እግረ መንገዱን የገበሬውን ልጆች፣ ጋዳፊና የአረብ ሀገር ከበርቴዎች ባስታጠቁት ዘመናዊ ታንክና መሣሪያዎች፣ እያጨደ በሬሳቸውና በደማቸው ላይ እየተረማመደ እንደነበር መሪር የቅርብ ትዝታ ነው። በቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ ይመራ የነበረው ጎጠኛው የወያኔ መንግሥት፣ የኢጣልያ ፋሺስት ያወጣውን በተለይ በአማራና በኦሮሞ ላይ ያነጣጠረውን የከፋፈለህ ግዛው ፖሊሲ ኮርጆ በመከተል፣ የአፄ ምኒልክ ሐውልት እንዲፈርስ ለማደረግ ሕዘቡን አነሳስቶ እንደነበር ይታወቃል።ሆኖም ሙከራው ወያኔ አስቦት በነበረበት ወቅት ባይሳካም፣ ሐውልቱን የማንሳት ሃሳብ አሁንም አለ። ስለዚህ ሕወሐት የሚመራው በውስጡ በሚስጥር በተሰገሰጉ ባንዳዎች እንደሆነ እያደር ሊታወቅ ስለቻለ የእምዬ ምኒልክ ወደጆች መዘናጋት የለባቸውም።
Ethiopian king Atse Menelik
ሐውልቱና ከኢጣልያን ጋር የተደረጉት ሁለት ከባድ ጦርነቶች
እምዬ ምኒልክ፣ እስከ አፍንጫው ድረስ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ በገፍ ታጥቆ ኢትዮጵያን ሊወር የመጣውን ጦር፣ አድዋ ላይ ገጥመው ወራሪውን ድባቅ መትተው አንፀባራቂ ድል ሲጎናፀፉ፣ ከሰሜን ሸዋ አብሮአቸው የዘመተው ስምንት ሺህ (8000) ፈረሰኛ የኦሮሞ ሚሊሽያ ሠራዊት በጦርነቱ ለተገኘው ድል ወሳኝ አስተዋፅዖ አድርጎ እንደነበረ በታሪክ የተመዘገበ የጀግንነት ሐቅ ነው። የአድዋው ድል የአውሮፓን ሀያላን መንግሥታትን አስደንግጦ ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሉአላዊ ነፃ ሀገር እንዲያውቋት አስገድዷቸዋል። ይህ ታላቅ የጥቁር ሕዝብ ድል በዓለማችን ላይ ለሚገኙት ጭቁን ጥቁሮች ሁሉ ሕያው ተስፋ ሰጥቷል።
በሽንፈቷ ሀፍረት የተከናነበችው ኢጣልያ፣ 40 ዓመት ሙሉ በሚስጢር ስትዘጋጅ ቆይታ፦ ሀ) በሚሊሽያዎቻችን ላይ ከሰማይ በአውሮፕላን የቦምብ ናዳ በማዝነብና በዓለም ሕግ የተከለከለውን መርዝ በመርጨት፤ ለ) በምድር በታንክና በመትረየስ የታገዘ መጠነ ሠፊ የሰለጠነ እግረኛ ጦር በማዝመት፤ ሐ) ሕዝቡን በጎሳ ከፋፍላ እርስ በርሱ በማጫረስ፤ መ) አማሮችና ኦሮሞዎች የሥልጣኔ ተፃራሪዎች ስለሆኑ ሌሎች ጎሳዎች በጠላትነት እንዲፈርጇቸው በመስበክ፣ አዲስ አበባን (ሸገርን) እንደ አውሮፓ ዘመን አቆጣጠር በ1936 ዓ.ም ለመቆጣጠር ችላለች። ዋቢ፦ Habešská Odyssea (YeHabesha Jebdu) የሃበሻ ጀብዱ by Adolf Parlesak Translated by Techane Jobre Mekonnen
የፋሺስትን ወረራ ያልተቀበሉት የኢትዮጵያ አርበኞች (በአዲስ አባባና በአካባቢው የሚገኙትን ኦሮሞዎችን ጨምሮ)፣ አራዳ ጊዮርጊስ በዳግማዊ ምኒልክ ሐውልት ዙሪያ ማታ ማታ እየተሰበሰቡ (ሬዲዮ አድማጭ መስለው) ይመካከሩ ነበር። ግራዚያኒ ይህን ሲሰማ ሐውልቱ እንዲነሳና በምሥጢር እንዲቀበር አዘዘ፤ በትእዛዙም መሠረት ሐውልቱ ተነስቶ ሌላ ጋ ተቀበረ። ፋሽስት ኢጣልያ ተሸንፎ ከሀገራችን ሲባረር፣ ሐውልቱ ከተቀበረበት ቦታ ተመልሶ እንደገና በቀድሞ ቦታው ላይ ሊተከል ቻለ።
ጠላት ተገዶ ያከበራቸውን እምዬ ምኒልክን ማክበር የምንኮራበት መብታችን ነው። እምዬ ምኒልክ ሲልቅ፣ የባንዳዎች ውላጅ ወያኔ ሲበሽቅ ሁሌ እደሰታለሁ። ምኒልክ አንድ ያደረጋትን ኢትዮጵያን ወያኔ ሲበታትናት አበክረን መቃወም የውዴታ ግዴታችን ነው። በዚህ ጉዳይ ለሚቃወሙን ተቺዎች መልሳችን ይሄው ነው።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር
አፄ ምኒልክ ከአንኮበር ወደ ሸገር ሲመጡ ያጋጠማቸው ተፋላሚ ቱፋ ሙና የተባለ ሐይለኛ የኦሮሞ ገዢ ነበር። አፄው ብልሀተኛ ስለነበሩ አማላጅ ልከው ታረቁና ቱፋ ሙናን ክርስትና አንስተው አበልጅ ሆኑ። የቱፋ ሙና ሰፊ ዘሮች እነ አቶ ብሩ ጎሮንቶ ገፈርሳ ግድብ አካባቢ በስተ ምዕራብ-ደቡብ አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ይኖሩ ነበር። አቶ ብሩን ባጋጣሚ ሱሉልታ አግኝቻቸው ከተዋወቅን በሗላ፣ ከባለቤቴ ጋር ገፈርሳ ድረስ እየሄድን እንጠይቃቸው ነበር። አቶ ብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ በተገኘበት በታላቅ ሥነሥርዓት ገፈርሳ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በተፈፀመው ቀብራቸውም ላይ ተገኝቻለሁ።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር (አዲሰ አበባ) የመጡት በኦሮሞ ባላባቶች የሚታዳደሩትን ግዛቶች አቋርጠው ነው። ቱፋ ሙና ብቻ ነው በነውጥ የተፋለማቸውና ውጊያው በእርቅ የቆመው። በነገራችን ላይ፣ የ1966ቱ አብዮት ሲፈነዳ እኔ አሰከማቀው ድረስ በሸዋ ውስጥ ሰፍኖ የቆየው ባላባታዊ ሥርዓት አራማጆች በአብዛኛው አለጥርጥር የኦሮሞ ተወላጆች ነበሩ።
የተወለድኩት አዲሰ አበባ ቀጨኔ ጋላ ሰፈር በሚባላው መንደር ውስጥ ነው። የከተማውን ዙሪያ ደህና አድርጌ አውቃለሁ። ሸዋ ውስጥ በልጅነቴ በእግሬና በፈረስ ከዚያም ስጎረምስ በመኪና በብዙ አቅጣጫዎች ተዘዋውሪያለሁ። ለምሳሌ፣ ከአዲስ አበባ ተነስተን እስከ 130 ኪሎሜትር ርቀት ዙሪያውን በወፍ በረር ብንቃኝ፣ የክልሉን ባላባትነት የአንበሳውን ድርሻ የኦሮሞ ተወላጆች ይዘውት እንደነበር አያከራክርም ለማለት ይቻላል። አፄ ምኒልክ የመሬት ግብር አስከፈሉ እንጂ የባላባቶችን የመሬት ይዞታ አለምክንያት አልነኩም። ዘውዱንም መሬቱንም እኔ ይዤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ሊቀረው ነው ብለው የመሬት ባለቤትነት በግል የእያንዳንዱ ዜጋ ይዞታ መሆን እንዳለበት በችሎት ላይ ስለመፍረዳቸው በአድናቆት ይነገርላቸዋል።

Monday, May 5, 2014

TPLF/EPRDF’s Divisive and Polarizing Political Master Plan is the Problem: Addis Ababa Master Plan is simply the Symptom


May 5, 2014
by Alem Mamo
The suffocatingly oppressive political rule of TPLF/EPRDF has continued to terrorize the people of Ethiopia, denying them their basic human rights to live in peace, dignity, and inclusive harmony. Since coming to power in 1991, the TPLF-led regime has implemented a deliberate system of permanent polarization and suspicion between and among communities. Obviously, the objective of this policy of permanent polarization and compartmentalized order is to weaken the ability of the Ethiopian people to resist and defeat this brutal totalitarian regime.
Addis Ababa Master Plan
The genesis and history of TPLF/EPRDF is deeply tied with its addiction to violence, murder, torture, and mass terrorization. The events of the last two weeks in Addis Ababa, Ambo, and other parts of the country are a clear testament of TPLF/EPRDF’s violent nature and it’s disregard for the sanctity and dignity of human life. First, there was the arrest of nine Zone 9 bloggers for no other reason than reporting and speaking truth to power. These young members of Zone 9 are representatives of their generation, committed to taking their rightful place in history. They knew all too well that the regime’s intolerance and even disdain for press freedom could make them a prime target. However, these young budding journalists/bloggers continued to inform the public and expose the crimes of the regime to the world, even if it meant going to jail and facing all physical and psychological suffering that comes with imprisonment. Their arrest has reaffirmed the fact of the TPLF/EPRDF regime’s unflinching commitment to keeping the people of Ethiopia under its clenched fist, and their fear of what Zone 9 bloggers/journalists are doing to report and resist. As the bloggers/journalists have articulated, there are two types of prisons in Ethiopia: the notorious Makalawi (which is divided into 8 zones) and prison dungeons spread all across the county; and the open-air prison which is the entire country (and where the name Zone 9 comes from). The bravery of these young bloggers/journalists is a profound lesson to all who fight for democracy, freedom, and justice, and their message is clear – freedom is not free!

Monday, April 28, 2014

ሠማያዊ ፓርቲ የነፃነት ትግልና የሃበሻ ጀብዱ

April 28, 2014

ዳኛቸው ቢያድግልኝ
በቅርቡ የሴቶችን ቀን አስመልክቶ በተደረገ የሩጫ ዝግጅት ወቅት የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችነ ነን ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች “አትለያዩን! አትከፋፍሉን! ነፃነት እንሻለን! ለድሃው ይታሰብለት! ኑሮ ከበደን! ውሃ ጠማን! መብራት ናፈቀን!” በማለት በጣም ሰብዓዊና እናታዊ ጥሪ ጮክ ብለው አሰምተው ነበር። ይህም መልካም ድርጊታቸው ለፍትህና ለአንድነት የሚደረግ ህዝባዊ ጥሪ በሚያስበርግጋቸው የወያኔ ባለስልጣናት ሁከት ፈጠራ ተብሎ ተወነጀሉ። ፕሮፌሰር አልማርያም በተቆጣው ብዕራቸው

… ያገሬ ወይዛዝርቶች በምህረት አልባ ጨካኞች ሲንገላቱና ሲወገሩ ከዳር ቆሜ ማየትን ህሊናዬ ፈጽሞ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም የእንግልታቸው ምክንያት ሰብዓዊ በሆነው መብታቸው ድምፃቸውን ስላሰሙ በመሆኑ የነሱና የመሰሎቻቸውን ጥሪ በዚህም ሳቢያ የሚደርስባቸውን አበሳ ሁሉ ለአለም አሳውቅ ዘንድ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ…

Semayawi party, ye habesha jebdu

ብለው ነበር። ከርሳቸው ድምጽ ጋር በማበር የሚያስተጋቡ ድምጾች ይኖሩ ዘንድ እውነት ነውና የኔንም ድርሻ እነሆ እጮሃለሁ። ጩሀቴም ቀደም ሲል በግፍ ለታጎሩ የህሊና እስረኞችና ሰሞኑን ለታፈሱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ደጋፊዎች አንዲሁም ለጎበዞቹ የዞን ዘጠኝ የሕዝብ አፈቀላጤዎችም (ብሎገሮችም) ነጻነት ያለኝ ጽኑ ፍላጎት መገለጫ ነው።
ሁከት ማለት የሌሎችን ሰላም ማደፍረስ፥ አምባጓሮና ጸብ ማንሳትና ማነሳሳት፥ የንብረት ጥፋትና በሰዎች ላይ አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳትን ማስከተል ነው። እኒህ ወጣት ሴቶች ግን ከዚህ በተቃራኒው የተንገላቱት ሰላም አንዳይደፈርስና ህዝብ እንዳይጎዳ በስልጣን ላይ ያሉት መንግስታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሰላማዊ ጥሪ ነበር ያቀረቡት። የሀሰት ፕሮፖጋንዳው ሰለባ ያልሆነ በሙሉ ወጣቶቹ በአንድነትና በፍትህ የጸናች ሀገር ለመረከብ ከዚህ የበለጠ ቢያደርጉም ተገቢ ነው የሚል ይመስለኛል። የነርሱ አሳሪዎች በነርሱ እድሜ ጠመንጃ አንስተው መጥፎ ነው ብለው የፈረጁትን መንግስት ለመዋጋት ጫካ መግባታቸውን አለመርሳት ብቻ ሳይሆን እንደትልቅ ገድል በየመድረኩና በየመጽሀፉ ሲናገሩና ሲያስነግሩ እንሰማለን። ታዲያ የዛሬው ትውልድ ያውም እንደነሱ ሰው ለመግደል ጠብመንጃ ሳያነሱ ፍትህ አይጉዋደል ብለው በሰላም መጠየቃቸው እንዴት መጥፎ ሁኖ ነው ለእስርና እንግልት የሚዳርጋቸው? ማሰርንና አፈናን እንደ የስልጣን ዘመን ማራዘሚያ አማራጭ አድርጎ መውሰድ ከሚያስብ አእምሮ ሳይሆን በፍርሃት ከተዋጠና ለውጥ አይቀሬ መሆኑን መቀበል ካቃተው ደካማ ጭንቅላት የሚመጣ ነው። በአንጻሩም ነገ የነርሱ የሆነው ወጣቶች በፍርሀት ተገንዘው አረመኔዎች ሀገራቸውንና ተስፋቸውን ሲያጠፉባቸው በዝምታ ሊያዩ አይቻላቸውም።

Ethiopia should immediately release bloggers (HRW)

April 28, 2014

Human Rights Watch
(Nairobi) – The Ethiopian authorities should immediately release six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26, 2014, unless credible charges are promptly brought.
Human Rights Watch on Ethiopia
United States Secretary of State John Kerry, who is scheduled to visit Ethiopia beginning April 29, should urge Ethiopian officials to unconditionally release all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials. The arrests also came days before Ethiopia is scheduled to have its human rights record assessed at the United Nations Human Rights Council’s universal periodic review in Geneva on May 6.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “The timing of the arrests – just days before the US secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech.”
On the afternoon of April 25, police in uniform and civilian clothes conducted what appeared to be a coordinated operation of near-simultaneous arrests. Six members of a group known as the “Zone9” bloggers – Befekadu Hailu, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabela – were arrested at their offices and in the streets. Tesfalem Weldeyes, a freelance journalist, was also arrested during the operation. Edom Kassaye, a second freelance journalist, was arrested on either April 25 or 26; the circumstances of her arrest are unclear but all eight individuals were apparently taken to Maekelawi Police Station, the federal detention center in Addis Ababa, the capital.

Wednesday, April 23, 2014

የወያኔዎች አስቂኝ መመሪያዎችና ዐዋጆች


April 23, 2014
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
በመጀመሪያ የክርስትና እምነት ተከታይ አንባቢዎች እንኳን ለ2006ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
ሕወሓት ወደ ሥልጣን መጥቶ በዓይነቱ የተለዬ የጥቁር አፓርታይድ ሥርዓትን በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ካቆመ ወዲህ እጅግ ብዙና ለመቁጠርም የሚያዳግቱ መመሪያዎችንና ዐዋጆችን ቀርፆአል፡፡ አንዳንዶቹን በዘፈቀደና በነሲብ እየቸከቸከ በፈለገው ሰዓትና ወቅት ራሱ ተግባራዊ በማድረግ፣ አንዳንዶቹንም ለማስመሰል ያህል በእንቅልፋምና ደናቁርት የ“ፓርላማ” አባላቱ አማካይነት በዐይን ጥቅሻ በሚታዘዝ የሆዳም ማይማን ጭብጨባ “አጸድቆ” ሥራ ላይ በማዋል ሀገርንና ሕዝብን ማተራመስ ከያዘ ሁለት ዐሠርት ዓመታትን ጨርሶ የሦስተኛውን ዐሠርት አንድ ሦስተኛ ያህል ጊዜ ለማገባደድ ጥቂት ወራት ብቻ ይቀሩታል፡፡
ከቅርቦች ልጀምር፡፡ ቅድም ቡና ስጠጣ እንዲህ የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡ እውነት ይሁን ሀሰት ገና አላረጋገጥሁም – ይሁን እንጂ የወያኔን ባሕርይ ለሚያውቅ ይህን ወሬ ሀሰት ነው ማለት የሚያስችል አዲስ ነገር አይገኝም፡፡ ከዚህ የበላለጡ አስቂኝና አስገራሚ መመሪያና ዐዋጆችን እየታዘብን 23 የመከራና ፍዳ ዓመታትን ስላቀናን ይህኛውን የተለዬ አያደርገውም፡፡ የሰማሁት ምን መሰላችሁ – ልማታዊ የወያኔ ሙዚቀኞችና ዳንኪረኞች በኮፒራይት መቸገራቸውን ስላመለከቱና ለዚህም ችግር መባባስ ትልቁን ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት የስልኮች ሚሞሪዎችና ብሉቱዝ በመሆናቸው እነዚህን አገልግሎቶች የሚሰጡ ማናቸውም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ መንግሥት ማገጃ አውጥቷል የሚል ነው፡፡ በዚህም ሳቢያ የእጅ ስልኮችና የመሳሰሉት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ማዕቀብ ሊጣልባቸው እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡ ለነገሩ ከኢትዮጵያ የወያኔ ሚዲያዎች በውዴታየ ስለራቅሁ ይህ መመሪያ በገሃድ ወጥቶ ይሁን አይሁን እስካሁን አላወቅሁም፡፡ በበዓሉ ምክንያት ከጎረቤት ውጪ ራቅ ወደሚል ሌላ ውጪ አልወጣሁም፡፡ ግን አይሆንም አይባልም፡፡ ወያኔ ከፈለገ “ከዛሬ ጀምሮ ከትግሬ በስተቀር ነጭ ጤፍ እንጀራ የሚበላና ጮማ የሚቆርጥ ሌላ የማኅበረሰብ ክፍል እንዳይኖር ዐውጃለሁ፤ ቢኖር ግን ህገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ እንደቃጣ ተቆጥሮ በአሸባሪነት የክስ ቻርጅ እስከሞት ሊደርስ በሚችል ከፍተኛ ቅጣት ዋጋውን ያገኛል፡፡” ብሎ ሊያውጅ ይችላል፡፡ ማንን ወንድ ብሎ ነው ወያኔ የፈለገውን ከማድረግ የሚቆጠበው? ወያኔ በምን ይዳኛል? በምንም፡፡ ለነገሩ ቀን የሰጠው ጅብ አንበሣንና ነብርን ሲቆረጣጥም ቢታይ ዘመኑ የትንግርት ነውና አያስገርምም፡፡ በኢትዮጵያም ሆነ በተቀረው ዓለም እየሆነ ያለውም ይሄውና ይሄው ብቻ ነው፡፡ ግን ግን በሀገራችን ለወደፊቱ ጅብ የማያሸንፍበትን ቀዳዳ መዝጋት የሚያስችለንን ታላቅ የሦስተኛው ሚሌንየም ሥልት መንደፍ እንደሚገባን ከወያኔው አዋራጅ የተፈጥሮ ልክስክስ ጠባይ የተማርን ይመስለኛል፤ የመንጌን አማርኛ ልጠቀምና ብታምኑም ባታምኑም የአፄውና የደርጉ ሥርዓቶች መንገዱን ባበጃጁለት ወያኔ ክፉኛ ተዋርደናል፡፡ አሸንፎ የማያውቅ ትንሽ ሰው እንዳያሸንፋችሁና መሣቂያና መሣለቂያ እንዳያደርጋችሁ በርትታችሁ ጸልዩ፡፡ ትንሽ ስል ማሸነፍን እንደህልም ይቆጥር የነበረ የባንዳዎችና የሥነ ልቦና ደዌ የተጣባቸው በበቀልና ጥላቻም የተሞሉ ዜጎች ውላጅ የሆኑ መለስን፣ ስብሃትንና ሣሞራን የመሰሉ የታሪክ አራሙቻዎች ማለቴ ነው፡፡ እንደነዚህ ያሉ ቀላሎች በታሪካዊ መደላድሎች መመቻቸት ምክንያት አንዳች ዕድል ካገኙ እንዴቱን ያህል ወጥ እንደሚረግጡና ነገሮችን በምን ያህል ደረጃ እንደሚያበለሻሹ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ለማንኛውም ሚሞሪ ያላቸው ስልኮችና መሰል ጋጄቶች ሊከለከሉ ነው አሉ፡፡ አልጋህ ውስጥ ተደብቀህም በሙዚቃ መቆዘም ሊቀር ነው፡፡ ኧረ ባል በሚስቱና ሚስትም በባሏ ቀረጥ እንዳይከፍሉ ያሰጋል፡፡ “እያንዳንድሽ ማን በሚገዛው ሀገር ውስጥ ተኝተሸ ዓለምሽን ትቀጫለሽ?” ብሎ ምቀኛው ወያኔ ለአንድ ግንኙነት ብር 50 ግብር ቢጥልና በየጉያችን ኤሌክትሮኒክ ሥውር ባልቦላ(ማይክሮቺብስ) እንደኖር ፕላንት ቢተክል ባለትዳሮች ምን ይውጠናል? ያቺው ብቸኛ መዝናኛችን ላይ ወያኔ በመብረቃዊ የማጥቃት እርምጃው ቢዘምትባት ወዴትና ለማንስ አቤት እንላለን? የሰይጣን ጆሮ ይደፈን፡፡ የምንተነፍሰውን አየርና የፀሐዩንማ በኑሮ ውድነቱ ላይ ጨምሮ ባልተወለደ አንጀት እያስገፈገፈን ነው፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተላለፈ ጥሪ!


April 23, 2014
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ለመሆኗ አለም ይመሰክርላታል፡፡ አንቱ የተባሉ ምሁራንን በማፍራት ለዓለም አበርክታለች፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአለም ካሉ ታላላቅ ዩንቨርስቲዎች እና የምርምር ተቋማት እስከ አመራነት ድረስ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መገኘታቸው ነው፡፡ እነዚህ ምሁራን በተሰማሩበት ስራ መስክ የሚያስመዘግቡት ውጤት እና በስራቸው ተሸላሚ መሆን ላነሳነው ሀሳብ ማጠናከሪያነት ያገለግለናል፡፡ እጅግ የሚያሳዝነውና ልብ የሚሰብረው ግን ሀገራችን ከእነዚህ ውድ ልጆቿ ተገቢውን ዋጋ አለማግኘቷ ነው፡፡ ሀገራችን የወላድ መካን እየሆነች ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሆነ ተብሎ የሚቀነባበር ሴራ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ብትሆንም ቅሉ በተከታታይ ስልጣኑን የጨበጡት ጭፍን አንባገነኖች በሚያራምዱት አግላይ ምሁር ፖሊሲ ምክንያት እውቀታችሁን እና ገንዘባችሁን በምትወዷት ሀገራችሁ ኢንቨስት አድታደርጉ ሁኔታዎች ባለመመቻቸታቸው የስደትን መራራ ጽዋ እንድትጨልጡ ተገዳችኋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተለይ ባለፉት 10 አመታት በተቃዋሚዎች መዳከም የሚያታግል ኃይል አጥታችሁ እንደቆያችሁም እናምናለን፡፡
ፓርቲያችን ሰማያዊ እያንዳንዱ ዲያስፖራ ሀገር ቤት ያለውን ዜጋ ያክል የኢትዮጵያዊነት መብት አለው ብሎ ያምናል፡፡ ይህ ይረጋገጥ ዘንድም አጥብቆ ይታገላል፡፡ በተለያየ ሁኔታና ወቅት አንባገነኖችን በሀገር ውስጥ እንደታገላችሁ እናምናለን፡፡ ለዚህ ትግላችሁና ለከፈላችሁት ዋጋም እውቅና እንሰጣለን፡፡ በስርዓቶቹ ጨካኝ ዱላ እና ሰቆቃ ብዛት ውድ ሀገራችሁን ትታችሁ የሥደትን ኑሮ ትገፉ ዘንድ ቢበየንባችሁም ስለ ኢትዮጵያ ከመብሰልሰል እንዳልዳናችሁና ሀሳባችሁ ሀገር ቤት ስለ መሆኑ መስካሪ አያሻም፡፡