Wednesday, October 30, 2013

ተስፋየ ገብረአብ እና የመከነ ብእሩ፡ ከቡርቃ ዝምታ እስከ የስደተኛው ማስታወሻ


October 29, 2013
መስፍን አማን
(ከሃርለም፣ኔዘርላንድ)

ከጥቂት ሳምንታት በፊት አንድ ቅዳሜ ሻይ ቡና ለማለት አምስተርዳም ከወዳጆቼ ጋር በነበረኘ ቀጠሮ ላይ እንደአጋጣሚ ተስፋየም በመሃላችን ተገኝቶ ነበር።የባጥ የቆጡን ስናወራ፣ስለአዲሱ የተፋየ መጽሃፍ አንስቶ የውይይታችንን አቅጣጫ ቀየረው።በመሃሉ ተስፋየ፣ከመጽሃፉ ውስጥ አንዳንድ የማልወዳቸው ምእራፎች ቢኖሩ ትችቶቹን የምቀበል ስለመሆኔ አስረግጦ ጠየቀኝ?።እኔም መጽሃፋን ካነበብኩት በሁዋላ ለጥያቄው መልስ ብሰጥ እንደሚሻል ገልጨለት በዛው ተለያየን። አይደርስ የለም መጽሃፉን ለህዝብ ከመበተኑ በፊት ረቂቁን አነበብኩት። ረቂቁን አንብቤ እንደጨረስኩ ለተስፋየ ጥያቄ መልስ መመለስ እንዳለብ ወሰንኩኝ። ይሁንና በቀድሞው ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ ተጽፎ የተሰራጨውን ጽሁፍ መውጣት ተከትሎ በዳያስፖራው አካባቢ አዋራው በመጨሱ ያዘጋጀሁትን ትችት በይደር ለማቆየት ወሰንኩ። በዚህ መሃል ተስፋየ ገብረአብ “የስደተኛው ማሰታወሻ” በማለት ያዘጋጀውን መጽሐፍ ባለፈው ሰሞን በነጻ አሰራጭቶልናል።
Tesfaye Gebreab Ethiopian author and writer
ተስፋዬ ገብረአብ
ወደ መጽሃፉ ትችት ስመለስ “በደራሲው ማስታወሻ” ውስጥ ያገኘሁት ደራሲ ኢህአዴግን ያገለግል ከነበረው ከቀድሞው ማንነቱ ያልተፋታውን ተስፋየ ገብረአብን ነበር። የእፎይታ መጽሄት ዋና አዘጋጅ እና የቡርቃ ዝምታ ደራሲን የድሮው ተስፋየን በዚህኛው የስነ-ጽሁፍ ስራ ውስጥም ዳግም አገኘሁት።የድሮው ተስፋየ ስል ታዲያ ስነጽሁፍን ለፍቅር፣ለመቻቻል፣እና ለእውቀት ሳይሆን የቆዩና የሻሩ ቁስሎችን መቆስቆሻ፣ያልነበሩትንም በመፍብረክ የእልቂት ነጋሪት መምቻ መሳሪያ አድርጎ የሚጠቀመውን ማለቴ እንደሆነ አንባቢ እንዲያስተውል
እፈልጋለሁ።”የስደተኛው ማስታወሻ” የነዛ ስራዎች ቀጣይ እንጂ በይዘቱም ሆነ በመልእክቱ ጭብጥ አዲስ የስነ- ጽሁፍ ስራ ነው ለማለት የማያስደፍሩ የብዙ ምእራፎችን አካቶአል። ለዚህ የማቀርበው ምክንያት ሃያስያኑ እንደሚሉት የገጸ-ባህሪ አሳሳሉና የመልእክቱ ጭብጥ አመራረጥ እንዲሁም እንደ ደራሲ በዋነኝነት ማስተላለፍ በፈለገው መልእክት ላይ ነው።

ኢህአዴግ የዘራውን አጨደ፣ ተጠያቂው ማን ነው?


እሳት አስነሳችሁ በሚል እስሩ ቀጥሏል
fire


በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ተቃውሞ ቢያቀርቡም የኢህአዴግን ጆሮ ማግኘት ያልቻሉ ተበዳዮች ርምጃ ወሰዱ። ሕዝብ ወዶና ፈቅዶ ያልተቀበለው ኢንቨስትመንት ከዘረፋ ተለይቶ እንደማይታይ የአካባቢው ነዋሪዎች አስታውቀዋል። ውድመት የደረሰበት የህንድ ኩባንያ በልማት ባንክ ላይ ኪሳራ ሊያስከትል እንደሚችል ስጋት አለ። ለደረሰው ጉዳት “ተጠያቂው ማን ነው?” የሚል ጥያቄ ተነስቷል። በጥርጣሬ የሚታሰሩ መበራከታቸው በክልሉ ባሉ ተመሳሳይ የእርሻ ኢንቨስትመንት ባለቤቶችን ስጋት ላይ ጥሏል።
ሻይ ቅጠል ለማልማት የተፈጥሮ ጥብቅ ደን እንዲያወድም የተፈቀደለት ቬርዳንታ ሀርቨስት የተባለ ኩባንያ በከፍተኛ ወጪ ያለማውና ለመለቀም በደረሰ ምርት ላይ ማንነታቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች እሳት ለቀውበታል። ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓም ደረሰ በተባለው ቃጠሎ ኩባንያው የደረሰበት ሊሳራ እስከ 80 ሚሊዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ስለ ጉዳዩ የሚያውቁ አስታውቀዋል።
አንጋፋ እድሜ ጠገብና ረዣዥም የተፈጥሮ ደን በመጨፍጨፍ ጣውላ እያመረተ ሲቸበችብ የነበረው ኩባንያ ሙሉ ንብረቱና ከፍተኛ መጠን ያለው የጣውላ ምርት ከተለያዩ ማሽኖች ጋር ወድሞበታል። የአካባቢው የጎልጉል ምንጮች እንዳሉት ኩባንያው ላይ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ ለመሰብሰብ የደረሰውን የሻይ ቅጠል ማሳ አጋይቶታል።

Friday, October 25, 2013

ሁሉም ይናገር ሁሉም ይደመጥ!! (ከአንተነህ መርዕድ እምሩ ቶሮንቶ)


October 24, 2013

ከአንተነህ መርዕድ እምሩ ቶሮንቶ
በቶሮንቶና ባካባቢው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለፈው እሁድ ኦክቶበር 13 ቀን 2013 ዓ ም ለሶስተኛ ጊዜ በደማቅ ሁኔታ በመሰባሰብ ኢሳትን የሚያጠናክር የገንዘብና ልዩ ልዩ ድጋፍ አድርገዋል። ወያኔ ከአገር አልፎ ውጭም የፈጠረውን ጊዜያዊ ፍርሃት ሰብሮ፣ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እንዲሰፍን የሚደረገውን ትግል ሁሉ ከወያኔ ባልተናነሰ በማደናቀፉ እርኩስ ተግባር የተካኑ የጨለማ ውስጥ ወገኖችም የፈጠሩትን አሉባልታ ከምንም ሳይቆጥር የመጣው ኢትዮጵያዊ ለአገሩ ነፃነት ማንኛውንም መስዋዕት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ያረጋገጠበት ነበር። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]
ESAT Toronto report
ESAT Toronto report, Abebe Gellaw, Berhanu Nega

Monday, October 21, 2013

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ

ዓለም ዓቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሚዋጋች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች ባለፈው ዓርብ በኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ይዞታ ላይ ያተኮረ በተለይም አዲስ ኣበባ በሚገኘው እና ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በእስረኞች ላይ ይፈጸማሉ ባላቸው ሰብዓዊ ሰቆቃዎች ላይ ያነጣጠረ አዲስ ሪፓርት ይፋ ኣድርገዋል።

Zu: Boss von mexikanischem Golf-Kartell festgenommen - Neuer Schlag gegen Drogenmafia
A relative of an inmate observes policemen behind the security fence after a riot inside Apodaca prison, on February 20, 2012, near Monterrey, state of Nuevo Leon, Mexico. At least 44 inmates have been killed during a riot Sunday and about 30 alleged members of the drug cartel Los Zetas were rushed out from the prison. AFP PHOTO/Julio Cesar Aguilar (Photo credit should read Julio Cesar Aguilar/AFP/Getty Images)
ሰብዓዊ መብት ሲባል በነገስታት መልካም ፈቃድ የሚቸሩ ወይንም መንግስታት ከሚመሩባቸው ህግጋተ መንግስታት የሚመነጩ ብቻ ሳይሆኑ በ ተ መ ድ የሰብዓዊ መብቶች ድንጋጌዎች መሰረት ሰዎች ሰው በመሆናቸው ብቻ በተፈጥሮ የተቀዳጁኣቸው መሰረታዊ የሰው ልጅ መብቶች ናቸው። በእነዚህ ህጎች መሰረት ደግሞ እንደ መኖ ኣልባሳት እና መጠለያ የመሳሰሉ የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቶችን ጨምሮ ዜጎች እንደ ህክምና እና ትምህርት የመሳሰሉ ማህበራዊ ፍላጎቶችን ሁሉ የማግኘት መብት ኣላቸው።
እናም ጥቂት ለማይባሉ ዓመታት እንዲያውም ዓስርተ ዓመታት ማለት ይቻላል በረኃብ አለንጋ ከሚገረፈው የኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር ለምን የሚል ጥያቄ ቢቀርብላቸው እንደ ምክኒያት አዲሶቹ መንግስታት በቀድሞዎቹ ላይ እያላከኩም ቢሆን መልሳቸው ግን ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል። ድህነት። በእርግጥ የፖሊሲ ችግሮች ሳይዘነጉ ከድህነት ወለል በታች በምትገኘው ኢትዮጵያ ኣምኖ ለመቀበል ማስቸገሩ ባይቀርም ኣይደለም ብሎ ለመከራከር ግን ሊከብድ ይችላል።
ሌሎች በርካታ የግል እና የቡድን መብቶች በገኃድ ሲጨፈለቁ እና በዚሁ ምክኒያት ሰዎች ሲታሰሩ ሲሰቃዩ እና ሲገደሉ ግን የሂዩማን ራይትስ ዎች የበላይ ኃላፊዎች እንደሚሉት በየኣጋጣሚዊ ከየኣቅጣጫው በተለያየ መልኩ ተቃውሞ እና ውግዘት ተለይቶት ኣያውቅም። ለዚህ ግን ባለስልጣናቱ ኣንድም እንደተለመደው ከጥያቄ መራቅ እና ኣሊያም ከእውነት የራቀ የፈጠራ ወሬ እያሉ ከመካድ ያለፈ ምላሽ የላቸውም የሚለው ሂዩማን ራይትስ ዎች ባሳለፍነው ሳምንት ማገባደጃ ላይም የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ይዞታ የሚያብጠለጥል አዲስ ሪፖርት ኣውጥተዋል።
ARCHIV - Ein Häftling in Guantanamo in Fußschellen. (am 27.04.2010von der US-Armee herausgegebenes Archivfoto). Seit zehn Jahren halten die USA Terrorverdächtige auf ihrem Marinestützpunkt Guantánamo Bay in Kuba fest. Nach den Anschlägen vom 11. September 2001 hatte US-Präsident George W. Bush dort die Errichtung eines Internierungslagers angeordnet. Sein Nachfolger Barack Obama beschloss zwei Tage nach seinem Amtsantritt im Januar 2009, das Camp binnen Jahresfrist zu schließen. Es war zum Symbol für Folter und Willkür geworden. Aus Obamas Versprechen wurde nichts. EPA/Michelle Shephard / POOL POOL PHOTO. EDS: IMAGE REVIEWED BY U.S. DEPARTMENT OF DEFENSE OFFICIAL PRIOR TO TRANSMISSION. (zu dpa-Themenpaket Guantanamo) +++(c) dpa - Bildfunk+++
በዚሁ ባለፈው ዓርብ ይፋ በሆነው እና 70 ያህል ገጾች ባሉት የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ መሰረት በኢትዮጵያ እስር ቤቶች በተለይም አዲስ ኣበባ በሚገኘው እና ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በሚገኙ እስረኞች ላይ ይፈጸማሉ የተባሉ ሰቆቃዎችን ለማጋለጥ ተሞክረዋል። ከሁሉም በላይ በሪፖርቱ መሰረት የፖለቲካ እስረኞች ግርፋት ወይንም ቶርችን ጨምሮ ፈታኝ በሆነ ኣያያዝ እየተሰቃዩ መረጃ እንዲአጡ ይደረጋሉ። የሐሰት ሰነድም እንዲፈርሙ ይገደዳሉ ተብለዋል። ይኸው መረጃ ኣንዳንዴ እስረኞቹ ተከሰው ችሎት በሚቀርቡበት ሳዓት እንደ ማስረጃ እንዲቀርብባቸው የሚደረግበት ኣጋጣሚም እንዳለ ተወስተዋል።

ኢትዮጵያ፡ በፖለቲካ እስረኞች ላይ የማሰቃየት ድርጊት ይፈጸማል


ፖሊስ በጋዜጠኞች እና በተቃዋሚዎች ላይ በደሎችን ይፈጽማል።
Maekelawi


(ናይሮቢ፣ ጥቅምት 7 ቀን 2006 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ባለስልጣናት አዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው ዋና የማሰሪያና የምርመራ ጣቢያ ውስጥ በፖለቲካ ሳቢያ የተያዙ  እስረኞችን እንደሚያሰቃዩ እና ለጎጂ አያያዝ እንደሚያጋለጡ ሂዩማን ራይትስ ዎች ዛሬ ይፋ ባደረገው ሪፖርት  አስታወቀ፡፡ ማዕከላዊ በመባል በሚታወቀው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሚፈጸሙ ህገ ወጥ ተግባራትን ለማስቆም እንዲሁም የሚፈጸሙትን በደሎች በተመለከተ የሚቀርቡ ቅሬታዎች በገለልተኛ ወገን እንዲመረመሩ እና አጥፊዎቹንም ተጠያቂ ለማድረግ የኢትዮጵያ መንግስት አፋጣኝ እርምጃ መውሰድ አለበት፡፡
74 ገፆች ያሉት እና “ ‘የሚፈልጉት የእምነት ቃል ነው’ ፡ ማሰቃየት እና ጎጂ አያያዝ በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ፖሊስ ጣቢያ” በሚል ርዕስ የወጣው ይኸው ሪፖርት ከ 2002 ዓ.ም ጀምሮ በማዕከላዊ የተፈፀሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች፣ በህገ ወጥ መንገድ የሚካሄድ ምርመራን እና በዚያ ያለውን አስከፊ የእስር  ሁኔታ ይዘረዝራል። በማዕከላዊ ከሚታሰሩት መካከል ተቃዋሚ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የተቃውሞ ሰልፍ አስተባባሪዎች እና ጎሳን መሰረት ያደረገ ትግል የሚያካሂዱ አማፂያንን ይደግፋሉ የሚባሉ ሰዎች ይገኙበታል፡፡ ሂዩማን ራይትስ ዎች ከ35 የሚበልጡ የቀድሞ ታሳሪዎችን እና ቤተሰቦቻቸውን ያነጋገረ ሲሆን እነሱም የማዕከላዊ ሃላፊዎች መረጃ እና የእምነት ቃል ለማግኘት ሲሉ እንዴት መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን እንደከለከሏቸው፣ እንዳሰቃዩአቸው፣ በተለያየ መልኩ ያልተገባ አያያዝ እንደፈጸሙባቸው እና የቤተሰብ አባላትን እና የሕግ ጠበቃ እንዳያገኙ እንደከለከሏቸው በዝርዝር ገልጸዋል፡፡
በሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ምክትል ዳይሬክተር ሌስሊ ሌፍኮ “መረጃ ለማግኘት ሲሉ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በዋና ከተማዋ እምብርት በየጊዜው ጥቃት ይፈፅማሉ” ብለዋል፡፡ ሌፍኮ እንዳሉት “ድብደባ፣ ማሰቃየት እና በማስገደድ ቃል መቀበል ለጋዜጠኞች እና ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የተገባ አይደለም።”
ሂዩማን ራይትስ ዎች እንዳለው በኢትዮጵያ ከ1997ቱ አወዛጋቢ ምርጫ በኋላ በሰላማዊ ተቃዎሞ ላይ የሚደረገው ጫና ተባብሷል። በማዕከላዊ  ተይዘው  ምርመራ የሚካሄድባቸው የመንግስት ተቃዋሚ ናቸው ተብለው የሚታሰቡ ሰዎች ጥብቅ በሆነው የሀገሪቱ የፀረ ሽብርተኝነት ሕግ መሠረት መከሰስን ጨምሮ የዘፈቀደ  እስር እና ፖለቲካን መሠረት ያደረገ ማሳደድ ይፈጸምባቸዋል።የማዕከላዊ ሃላፊዎች በዋናነትም መርማሪ ፖሊሶች እስረኞቹን በተለያየ መንገድ ያሰቃያሉ፤ ጎጂ አያያዝም ይፈጽማሉ፡፡ በተለይ በምርመራ ጊዜ ታሳሪዎቹ በጥፊ፣ በእርግጫ እንዲሁም በብትር እና በሰደፍ በተደጋጋሚ እንደተመቱ ለሂዩማን ራይትስ ዎች ገልጸዋል፡፡ እስረኞቹ ሰውነታቸውን ለህመም በሚዳርግ ሁኔታ እንዲሆኑና በተለይም እጆቻቸውን ከግድግዳ ጋር ታስረው እንዲንጠለጠሉ ተደርጎ ለረጅም ሰዓታት ያለማቋረጥ እንደሚደበደቡ ተናግረዋል። ከኦሮሚያ ክልል የመጣ አንድ ተማሪ  ብቻውን ተነጥሎና በሰንሰለት ታስሮ ለበርካታ ወራት እንዲቆይ እንደተደረገ ተናግሯል፡፡ “ለመቆም ስሞክር እቸገራለሁ፡ ለመቆም ጭንቅላቴን፣ እግሮቼን እና ግድግዳውን መጠቀም ነበረብኝ ፡፡ ምግብ ስመገብ እንኳ በሰንሰለት ታስሬ ነበር። ስመገብ እጆቼ  በፊት ለፊት በኩል እንዲታሰሩ ይደረጋል ስጨርስ ደግሞ መልሰው ወደ ኋላ ያስሩኛል።”

Friday, October 18, 2013

ስንቱን አጣን!



የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ!

deforested
እንደኢትዮጵያ ባለ ኋላቀር አገር አገር ውስጥ መሠልጠን ብዙ ችግር አለበት፤ እኔ ራሴ በኮምፒዩተር መጻፍ ከጀመርሁ ሠላሳ ዓመት ሊሆነኝ ነው፤ ታዲያ መብራት ጠፋና የምሠራው ባጣ የቆዩ ወረቀቶችን ሳገላብጥ አንድ እአአ በዲሴምበር 26 1965 ከዱሮ ተማሪዬ የተጻፈልኝን ደብዳቤ አገኘሁ፤ በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በነበረ ከአንድ በጣም ጎበዝ ወጣት የተላከልኝ ነበረ፤ ከተመረቀ በኋላ በአንድ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ ለጥቂት ዓመታት ሠርቶ ትምህርቱን ለመቀጠል ወደአሜሪካ ሄዶ በሎዝ አንጄለስ አካባቢ ከሚገኝ ትምህርት ቤት ገብቶ ነበር፤ ደብዳቤውን የጻፈልኝ ከዚያ ነው፤ ደብዳቤው ሰባት ገጾች አሉት፤ ከሰባቱ ገጾች አምስቱ ስለኢትዮጵያ ያለውን ስጋት የሚገልጽ ነው፤ በሎዝ አንጀለስ አካባቢ ካሉ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ ብዙዎቹ የሚያሳዩት የመንደረኛነት ስሜት እያበሳጨው የተማሩት ሰዎች በእንደዚህ ያለ ማኅበረሰባዊ ኋላቀርነት ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያ የምትባለው አገር እንዴት መራመድ ትችላለች? እያለ ይሰጋ ነበር።
ደብዳቤውን ላቋርጥና ስለሰውየው ትንሽ ልናገር፤ ተማሪ ሆኖ ክፍል ውስጥ ምንም ነገር የማያሳልፍ በጣም ተከራካሪ ተማሪ ስለነበረ አደንቀው ነበር፤ አንድ ጊዜ እንዲያውም የዘውድ መንግሥት ደጋፊ ነኝ አልሁና አንዴት በትከሻው ላይ ጭንቅላት ያለው ሰው ዓመቱን በሙሉ የዘውድ አገዛዝ የሚያደርስብንን በደልና ችግር ሲነግረን ቆይቶ አሁን ደግሞ ያንን ደጋፊ ነኝ ይላል ብሎ ወረፈኝ፤ ልጁን ስለማውቀው አነጋገሩ አሳቀኝ እንጂ አላስቆጣኝም፤ ጥያቄህ ይገባኛል፤ ግን እኔን ሳትወርፈኝ መጠየቅ ትችል ነበር በዬ ቢቀበለውም ባይቀበለውም ለጥያቄው መልሱን ሰጠሁት፤ በኋላም ጥሩ ጓደኛዬ ነበር።

እባብ ለእባብ፣ ይተያያል በካብ


October 16, 2013


ከወንድሙ መኰንን፣ ለንደን
ወዲያማዶሁኖአንድሰውተጣራ
ወዲህማዶሁኖሌላሰውወይአለው
ጎበዝአንድበሉይኽነገርለኛነው።
የለንደኑ ጸረ-ሕዝብ አመጸኛ፣ አንድ እርምጃ ሲወስዱ፣ ሕዝቡ ሁለት እርምጃ ቀድሞአቸው ይጠብቃቸዋል። ሲበዛ ተንኰለኛ በመሆናቸው፣ አንድ ቀን ተሳስተውም ደግ ነገር ሠርተው ቢገኙ፣ የሚያምናቸው ሰው አይኖርም። በዓይነ ቁራኛ ነው እንቅስቃሴአቸውን የምንቆጣጠረው። በዕውነት ተጸጽተው እንኳን ቢያለቅሱ፣ የአዞ ዕምባ ብሎ ነው ሰው የሚሸሻቸው። አሁንም ተነቃቅተናል።
London Ethiopian Orthodox church controversy
አባ ተባዩ አስመሳይ መነኵሴ፣ የሚጠቅማቸው መስሎአቸው፣ ለወየኔ የመሽሎኪያ ቀዳዳ አበጀተውለት አስጠቁን። “የአስተዳደር መዋቅሩ አይሻሻልም፣ እኔም ከሥልጣኔ አልወርድም” – እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል ሁኖባቸው ለወያኔ ወደው ገብተው እኛን በሶልዲ ሸጡን። ከአፈርኩ አይመልሰኝ ሁኖባቸው ነው መሰለኝ፣ የወያኔን ሴራና ሸር የምንቃወምዉን በሙሉ፣ የደርግ ባለሥልጣኖች ብለውን፣ በጠራራው ሜዳ ላይ በቪዲዮ እየተቀዱ “ንጉሳቸውን የገደሉ! ፓትርያርካቸውን የገደሉ![1]  ብለው ተሳልቀውብን ለወያኔ ታማኝነታቸውን አረጋገጡ።  እነዚህናን የመሳሰሉትን የየጊዜውን ክስተቶች ብዙ ጸሐፊዎች፣ እኔም እንዳቅሚቲ ፣ ጭብጡን አያይዘናችኋል። ነገሩ አሁን አክርረው፣ በጣም አስቀያሚ አድርሰው አደገኛ የሆነ ፍልሚያ ቅዳሜና እሑድ 12th and 13th October 2013 ጠንሠው ተጋፍጠን ተርፈናል። እግዚአብሔር የመስገን!

Wednesday, October 16, 2013

‘Freedom on the Net’ report says Ethiopia among the least free

October 16, 2013

According to the ‘Freedom on the Net 2013′ report, Ethiopia has been labeled as “least free” and ranked 79 from 100; 1 being the most free and 100 the least free. The report states that Ethiopia has one of the lowest internet and mobile telephone penetrations in the world as inadequate infrastructure, government monopoly over the telecom sector, and obstructive telecom policies have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs).

ለአፍሪካ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች ፍትሕ አይቀሬ ናት


October 16, 2013

ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ

ማስታወሻ ለአንባቢው፡፡ ባለፈው ሳምንት ሐተታዬ ‹‹የዘር አደን›› በሚል አሉባልታዊ ክስ  የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በተሰነዘረበት ክስ ደግፌው ተሟግቼለታለሁ፡፡ በዚህም ሳምንት ድጋፌን በመቀጠል እነዚህ ፈላጭ ቆራጭ ገዢዎች የፈጠሙትን ግፍና በደል ጭቆና በመዘርዘር ራሳቸውን ነጻ በማድረግ የአይ ሲ ሲን (የኣለም ወንጀለኛ ፍርድ ቤት) ስም በማብጠልጠልና የቆመለትን ዓላማ የሳተ በማስመሰል ገዢዎችና አስፈጻሚዎ ቡችሎቻቸው ያነሱዋቸውን ማስረጃ ቢስ ውንጀላዎች በተጨባጭ ማስረጃ ድርጊቶታቸውንና ሸፍጣቸውን ይፋ ለማድረግ ወስኛለሁ፡፡ የኦክቶበር 11-12, 2013 የአፍሪካ አንድነት ‹‹መሪዎች›› የጨረባ ስብሰባ የተጠራውም ቴአትራዊ የልብ ወለድ ሴራ ለማካሄድና ነጻ ለመምሰል የሚያስችላቸውን ቅጥፈት ለማናፈስ ነው፡፡
international criminal court
በኔ እምነት አይ ሲ ሲ የዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብት ሕግጋት ትክክለኛውና ጠንካራው ምልክት ነው፡፡ አይ ሲ ሲ ላለፉት ጥቂት ዓመታት ስራውን በማከናወን ላይ ነው፡፡እስካሁን ያስመዘገባቸው ውጤቶች ጥቂት ቢሆኑም ለወደፊቱ ግን ያሻቸውን በደልና ግፍ ፈጥመው ግድያና አስገድዶ መድፈርን ሰብአዊ መብት በደልን አዘው በማስፈጸም በሥልጣናቸውም አላግባብ ባልገውና ተጠቅመው፤ ሃገርን አራዉተው፤ ሕዝብን በበደልና ግፍ ጫና አጉብጠውና አንበርክከው፤ በነጻ ሲቀመጡና ሲንደላቀቁ የነበሩትን እያጋለጠ ለፍርድ ለማቅረብ የሚችል ጠንካራ ተቋም እንደሚሆን እምነቴ ነው፡፡  የአፍሪካ ጨቋኝና የግፍ በደል ባለቤት የሆኑት ገዢዎች በሕዝቡ ላይ ሊኩራሩና ሊደነፉ፤ የሕግ የበላይነትን በመጨፍለቅ ሊቀጥሉ ይጥሩ ይሆናል፤ አሁን ግን አይ ሲ ሲ ስለመጣባቸውና ለሕዝቡ ወግኖ ስለቆመ ስሙ በተጠራ ጊዜ እየተርበደበዱና መግቢያ እያጡ በመሄዳቸው የአይ ሲ ሲን ስም በማጉደፍ ነጻ ለመሆን ቢጥሩ መንገድ ሁሉ፤ በደላቸው ሁሉ፤ ግፋቸው ሁሉ አይ ሲ ሲን እየቀሰቀሰባቸው በመሆኑ ኦክቶበር 13 2013 የቁም ተዝካራቸው ማውጫ አድርገው ሊሰባሰቡ ነው፡፡
በኦክቶበር 11-12,  2013 አድመኞቹ የአፍሪካ ‹‹መሪዎች›› አስተጋቢው የእንግዳ መቀበያ የአፍሪካ አዳራሽ በመሰባሰብ አብዛኛዎቹ በሮም ከጸደቀው ደንብ (አለም ኣቀፍ ዉል) በመውጣት በደስታ ተሞልተው የዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤትን የሞት ውሳኔ ያስተላልፋሉ፡፡ ቀብሩንም ለማስፈጸም የኢትዮጵያ የይስሙላ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአፍሪካ  አንድነት ተዘዋዋሪ የ2013ቱ ሊቀመንበር ሃይለማርያም ደሳለኝ ነው፡፡ ስብሰባውንም ሲከፍት ‹‹ዛሬ በዚህ የምጽዋት አዳራሻችን የተሰባሰብነው አይ ሲ ሲን ለማወደስ ሳይሀሆን ልንቀብረው ነው….›› በማለት ይሆናል፡፡ የዚህ የቀብር ጥድፍም ሰበቡ የኬንያው ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኬንያ በተካሄደው የ2007 ምርጫ ወቅት በፈጸመው የሰብአዊ መብት ግፍ ለመጠየቅ ኖቬምበር 12 2013 ለፍርድ ሊቀርብ በመሆኑ ነው፡፡ በተመሳሳይ ወንጀልም ምክትሉ ዊሊያም ሩቶ ፍርዱ በሄይግ የዓለም አቀፍ የወንጀል ፍርድ መታየት ከጀመረ ሁለተኛ ወሩ ነው፡፡ የአፍሪካ አንድነት በኬንያታ እና በሩቶ ላይ የተመሰረተውን ክስ ዘዴ ፈልጎ ካላነሳ በስተቀር ‹‹የኑክሊየር ፈንጂ መቃወሚያውን›› በመጠቀም ከአይ ሲ ሲ አባልነት ለመውጣት እንደሚችልም በማስፈራራት ላይ ነው፡፡

Tuesday, October 15, 2013

ስንቱን አጣን! (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

October 14, 2013


እንደኢትዮጵያ ባለ ኋላቀር አገር አገር ውስጥ መሠልጠን ብዙ ችግር አለበት፤ እኔ ራሴ በኮምፒዩተር መጻፍ ከጀመርሁ ሠላሳ ዓመት ሊሆነኝ ነው፤ ታዲያ መብራት ጠፋና የምሠራው ባጣ የቆዩ ወረቀቶችን ሳገላብጥ አንድ እአአ በዲሴምበር 26 1965 ከዱሮ ተማሪዬ የተጻፈልኝን ደብዳቤ አገኘሁ፤ በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በነበረ ከአንድ በጣም ጎበዝ ወጣት የተላከልኝ ነበረ፤ ከተመረቀ በኋላ በአንድ ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ ለጥቂት ዓመታት ሠርቶ ትምህርቱን ለመቀጠል ወደአሜሪካ ሄዶ በሎዝ አንጄለስ አካባቢ ከሚገኝ ትምህርት ቤት ገብቶ ነበር፤ ደብዳቤውን የጻፈልኝ ከዚያ ነው፤ ደብዳቤው ሰባት ገጾች አሉት፤ ከሰባቱ ገጾች አምስቱ ስለኢትዮጵያ ያለውን ስጋት የሚገልጽ ነው፤ በሎዝ አንጀለስ አካባቢ ካሉ ኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት በሚያደርግበት ጊዜ ሁሉ ብዙዎቹ የሚያሳዩት የመንደረኛነት ስሜት እያበሳጨው የተማሩት ሰዎች በእንደዚህ ያለ ማኅበረሰባዊ ኋላቀርነት ውስጥ ሆነው ኢትዮጵያ የምትባለው አገር እንዴት መራመድ ትችላለች? እያለ ይሰጋ ነበር።
Prof. Mesfin Woldemariam
Prof. Mesfin Woldemariam
ደብዳቤውን ላቋርጥና ስለሰውየው ትንሽ ልናገር፤ ተማሪ ሆኖ ክፍል ውስጥ ምንም ነገር የማያሳልፍ በጣም ተከራካሪ ተማሪ ስለነበረ አደንቀው ነበር፤ አንድ ጊዜ እንዲያውም የዘውድ መንግሥት ደጋፊ ነኝ አልሁና አንዴት በትከሻው ላይ ጭንቅላት ያለው ሰው ዓመቱን በሙሉ የዘውድ አገዛዝ የሚያደርስብንን በደልና ችግር ሲነግረን ቆይቶ አሁን ደግሞ ያንን ደጋፊ ነኝ ይላል ብሎ ወረፈኝ፤ ልጁን ስለማውቀው አነጋገሩ አሳቀኝ እንጂ አላስቆጣኝም፤ ጥያቄህ ይገባኛል፤ ግን እኔን ሳትወርፈኝ መጠየቅ ትችል ነበር በዬ ቢቀበለውም ባይቀበለውም ለጥያቄው መልሱን ሰጠሁት፤ በኋላም ጥሩ ጓደኛዬ ነበር።
ከአሜሪካ ትምህርቱን ጨርሶ እንደመጣ ተገናኘንና ወደቀድሞ ሥራው ወደወንጂ ተመልሶ እንደሆነ ስጠይቀው ‹‹እንዴት ብዬ! ዕድሜ ልኬን የፈረንጅ አሽከር ሆኜ መኖር አልፈልግም፤ አሁን ደግሞ ያስተማረኝን ሕዝብ ላገልግል እንጂ!›› ነበር ያለኝ፤ በመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና በወንጂ ባሉት ደመወዞች መሀከል ከፍተኛ ልዩነት ነበረ፤ ቁም-ነገረኛነቱን፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያለውን ታማኝነት፣ የግል ጥቅሙን ቀንሶ ኢትዮጵያን ለመርዳት ባሳየው ተግባራዊ አርአያነት የማደንቀው የወታደር ልጅ ነው።

እንደሃገር እንነጋገር!

October 15, 2013


ታደለ መኩሪያ
ኑር ከሰው ኑር ከሃገር ይል ነበር፡ የሃገሬ ሰው፤ ሰው ለሰው መፈጠሩን የሚገልጽ አባባል ነው። በአጠገብህ ካለው መሰልህ ሰው አብረህ መኖር ከቻልክ በመላው ሃገርህ ካለው ሰው መኖር አያቅትህም ለማለት ነው።
የሰው ልጅ ለራሱ መልካሙን እንደሚያስብና እንደሚሰራ ሁሉ ራሱን ለማጥፋትም የዛኑ ያህል ይሠራል። ጥያቄው ባብላጫው ለየትኛው ይሠራል ነው? ሕዝብ እንደ አንድ የሃገር ዜጋ ተሰባስቦ ሲኖር ማሟላት ያለበት በተፈጥሮ የተቀበለው ግዴታ አለበት። መሠረታዊ የሆኑ ፍላጎቶቹን ማሟላት፣ ስብዕናውን ያለማስደፈር፣የሌላውንም ያለመድፈር፣በሌላው ላይ ፍትህ ሲጓደል የእርሱም እንደተጣሰ መቁጠር፤ ትውልድ እንዲተካው ሲያስብም ቅርስ ማስተላለፍም  ግድ እንሚለው ማወቅ  ከብዙቹ ጥቂቶቹ ናቸው። ያ ሣይሆን ቀርቶ ዜጎች በረሃብ፣ በጦርነት፣በስደት፣ በፍትህ እጦት የሚጎሣቆሉ ከሆነ ሰው አውቆም ሆነ ሣያውቅ ለመልካሙ ሣይሆን ለጥፋቱ እየሰራ ነው። በግብተኝነት መሪዎች ናቸው ለዚህ ሁለ ጥፋት ተጠያቂዎች በማለት የሚያቀርበው ከሃላፊነት የማምለጫ ምክንያት ውኃ አያነሳም፤ ለምን ቢባል መሪ ከሕዝብ ነውና የሚወጣው፤ ሆኖም ወደዝርዝር ሐታታ ከመግባቴ በፊት ለአንባቢዬ ጥያቄ ላቅርብ፤ በኢትዮጵያ ሃገራችን የመልካሙ ሥራ ወይስ የጥፋቱ ሥራ አይሎ ይገኛል? መልሱን ለእናንተ ለተወው።
ከኖርኩት ዘመን ልጀምር፣ ከአርባ ዓመት በፊት የሕብረተሰባችን አመለካከት፣ የተፈጥሮ ሐብታችን  አጠባበቅ አሁን ካለንበት  በጥልቀት ሲመረመር፣ ሰው ራሱን የሚያጠፋ እንጂ የሚያለማ ተግባሩ ጎልቶ አይታይም ። በሰዎች መካከል የነበረው መከባበር፣ የሃይማኖት ዕምነት፣የቃልኪደን ጽናት እየተሟጠጠ መምጣቱን ያሣያል። የተፈጥሮ ሐብታችንም በቁማር እንደተገኘ ሐብት በአስረሽ ሚቺው የመሰለ የዜግነት ሃላፊነት በጎደለው መንገድ መውደሙ ይታያል። ሰው ራሱ በሰራው ጥፋት  ምን ማድረግ እንዳለበት ግራ ተጋብቷል። በቅርቡ ዶክተር በረሃኑ ነጋ ‘ዴሞክራሲና ሁለንታዊ ልማት በኢትዮጵያ’ በሚል ርዕስ ባሳተሙት መጽሐፋቸው ውስጥ ሃገራችን ያለችበትን አስጊ ሁኔታ ገልጸዋል። በጥናት የተገኙ መረጃዎችን ዋቢ በማድረግ ለናሙና ያህል ያሉትን ኩነቶች በመጽሐፉ ውስጥ አስፍረዋል። የሰው ልጅ ራሱን ከሚያጠፋው ተግባሩ ይልቅ ከሚያለማው ሥራ ላይ ልቆ ቢገኝ እሰየው ነበር፤ ግን አልሆነም። እንዲሆን ምን መደረግ አለበት? ለሚለው መልሱ  እንደሃገር ከመነጋገር  ሌላ አማራጭ የለውም። ሰው ለሃገሩ ልማትም ሆነ ጥፋት ሃላፊነት አለበት። እያነዳንዱ ሰው ትውልድ እተካባታለሁ የሚላትን ሃገሩን ካልተከባከበ ለተፈጥሮ ሐብቷ መከበር ዘብ ካልቆመ ከዚያ ውጭ የሚሠራው ለጥፋት ነው። በዴሞክራሲ የተመረጡ የሕዝብ ተወካዮች የማይመሩት አስተዳደር የሚሠራው ለጥፋት ነው። በዘፈቀደ  በነዝህላልነት በልምድ የሚሠሩ ሥራዎች የሚመሩት ወደ ጥፋት ነው።

Saturday, October 12, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወሰዱ

October 11, 2013


በአሁኑ ወቅት በመነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር የነበሩት የፓርቲ አመራሮች ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መወሰዳቸዉን አሁን የደረሰን መረጃ ይገልፃል፡፡
***
ጉዳዩ እንደዚህ ነው መንግስት ነኝ ባዩ በስራው ግን ከማፍያ ቡድን እምብዛም የማይለየው ህወሀት/ኢህአዴግ በተለየም የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ አጠናክረው የቀጠሉት የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ ይህን ህዝብ ውስጥ በፍጥነት እየሰረጸ የመጣውን እንቅስቃሴ ድምጽ በሌለው መሳሪያ ለማዳከምና ብሎም ለማምከን ህወሀት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ስልት ቡድኑ ምን ያህል “የሞራል የበታችነት” እንደተላበሰ የሚያሳይ ነው።
የሰማያዊ ፓርቲ የካቲት 12(መነን) አካባቢ አዲስ የተከራየውን ጽህፈት ቤት ለመረከብ ጥቅምት 1/2006 ዓ.ም በቦታው ይገኛል። ይሁንና ቀድመው በቦታው የተገኙ የህወሀት/ኢህአዴግ ሰዎች ቤቱን እኛ ቀደም ብለን የተከራየነው ስለሆነ የሚገባው ለኛ ነው በማለት ወዝግብ ያነሳሉ… እንግዲህ አንባብያን እራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው ሀይል የሰፈር “ጢቦ” ሆኖ መጣ ማለት ነው…

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወሰዱ

October 11, 2013


በአሁኑ ወቅት በመነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር የነበሩት የፓርቲ አመራሮች ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መወሰዳቸዉን አሁን የደረሰን መረጃ ይገልፃል፡፡
***
ጉዳዩ እንደዚህ ነው መንግስት ነኝ ባዩ በስራው ግን ከማፍያ ቡድን እምብዛም የማይለየው ህወሀት/ኢህአዴግ በተለየም የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ አጠናክረው የቀጠሉት የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ ይህን ህዝብ ውስጥ በፍጥነት እየሰረጸ የመጣውን እንቅስቃሴ ድምጽ በሌለው መሳሪያ ለማዳከምና ብሎም ለማምከን ህወሀት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ስልት ቡድኑ ምን ያህል “የሞራል የበታችነት” እንደተላበሰ የሚያሳይ ነው።
የሰማያዊ ፓርቲ የካቲት 12(መነን) አካባቢ አዲስ የተከራየውን ጽህፈት ቤት ለመረከብ ጥቅምት 1/2006 ዓ.ም በቦታው ይገኛል። ይሁንና ቀድመው በቦታው የተገኙ የህወሀት/ኢህአዴግ ሰዎች ቤቱን እኛ ቀደም ብለን የተከራየነው ስለሆነ የሚገባው ለኛ ነው በማለት ወዝግብ ያነሳሉ… እንግዲህ አንባብያን እራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው ሀይል የሰፈር “ጢቦ” ሆኖ መጣ ማለት ነው…

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወሰዱ

October 11, 2013


በአሁኑ ወቅት በመነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር የነበሩት የፓርቲ አመራሮች ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መወሰዳቸዉን አሁን የደረሰን መረጃ ይገልፃል፡፡
***
ጉዳዩ እንደዚህ ነው መንግስት ነኝ ባዩ በስራው ግን ከማፍያ ቡድን እምብዛም የማይለየው ህወሀት/ኢህአዴግ በተለየም የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ አጠናክረው የቀጠሉት የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ ይህን ህዝብ ውስጥ በፍጥነት እየሰረጸ የመጣውን እንቅስቃሴ ድምጽ በሌለው መሳሪያ ለማዳከምና ብሎም ለማምከን ህወሀት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ስልት ቡድኑ ምን ያህል “የሞራል የበታችነት” እንደተላበሰ የሚያሳይ ነው።
የሰማያዊ ፓርቲ የካቲት 12(መነን) አካባቢ አዲስ የተከራየውን ጽህፈት ቤት ለመረከብ ጥቅምት 1/2006 ዓ.ም በቦታው ይገኛል። ይሁንና ቀድመው በቦታው የተገኙ የህወሀት/ኢህአዴግ ሰዎች ቤቱን እኛ ቀደም ብለን የተከራየነው ስለሆነ የሚገባው ለኛ ነው በማለት ወዝግብ ያነሳሉ… እንግዲህ አንባብያን እራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው ሀይል የሰፈር “ጢቦ” ሆኖ መጣ ማለት ነው…
ይህ በዚህ እንዳለ ነው አሁን በቅርቡ የክፍለ ከተማዉ ፍትህ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ጌታሁን አማረ ፤ የወረዳዉ አስተዳደር ሃላፊዎች ፤- የወረዳ 3 ስራ አስፈፃሚ አቶ አማረ ቤካ ፤ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ አማረ አቡጤ ፤ መነን አካባቢ ፖሊሶች ፤ ፌደራል ፖሊሶች እና ሲቪል የለበሱ የደህንነት አካላት በጋራ በመሆን ኢንጅነር ይልቃልን ጨምሮ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችችን ወደ ወደ መነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወሰዷቸው።
የሰማያዊ ፓርቲ ሁኔታውን እንዲህ በማለት በፌስ-ቡክ ገጹ ላይ ጠቅሶታል፣

Friday, October 11, 2013

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ወደ ፖሊስ ጣብያ ተወሰዱ


October 11, 2013



በአሁኑ ወቅት በመነን አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር የነበሩት የፓርቲ አመራሮች ወደ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ መወሰዳቸዉን አሁን የደረሰን መረጃ ይገልፃል፡፡
***
ጉዳዩ እንደዚህ ነው መንግስት ነኝ ባዩ በስራው ግን ከማፍያ ቡድን እምብዛም የማይለየው ህወሀት/ኢህአዴግ በተለየም የሰማያዊ ፓርቲ እና የአንድነት ፓርቲ አጠናክረው የቀጠሉት የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።
“ሳይቃጠል በቅጠል” እንዲሉ ይህን ህዝብ ውስጥ በፍጥነት እየሰረጸ የመጣውን እንቅስቃሴ ድምጽ በሌለው መሳሪያ ለማዳከምና ብሎም ለማምከን ህወሀት/ኢህአዴግ እየተከተለ ያለው ስልት ቡድኑ ምን ያህል “የሞራል የበታችነት” እንደተላበሰ የሚያሳይ ነው።
የሰማያዊ ፓርቲ የካቲት 12(መነን) አካባቢ አዲስ የተከራየውን ጽህፈት ቤት ለመረከብ ጥቅምት 1/2006 ዓ.ም በቦታው ይገኛል። ይሁንና ቀድመው በቦታው የተገኙ የህወሀት/ኢህአዴግ ሰዎች ቤቱን እኛ ቀደም ብለን የተከራየነው ስለሆነ የሚገባው ለኛ ነው በማለት ወዝግብ ያነሳሉ… እንግዲህ አንባብያን እራሱን መንግስት ብሎ የሚጠራው ሀይል የሰፈር “ጢቦ” ሆኖ መጣ ማለት ነው…

Sunday, October 6, 2013

የምርትና የሕዝብ እድገት እሽቅድድም


መሬት የማነው? ክፍል ሁለት ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
farmer1


እአአ በ1798 (ከሁለት መቶ አሥራ አምስት ዓመታት በፊት) መምሬ ቶማስ ሮበርት ማልቱስ የሚባል የ32 ዓመት የብሪታንያ ቄስ የዘመኑን የነገረ ንዋይ አስተሳሰብ የለወጠ አዲስ ሀሳብን የያዘ መጽሐፍ አሳተመ፤  ሀሳቡ በጣም ግልጽ ነበረ፤ የሰው ልጆች ቁጥር እድገት መጠኑ እያጠፈ የሚሄድ ነው፤  የሕዝብ ቁጥር 1፣ 2፣ 4፣ 8፣ 16፣ 32፣ 64፣ 128፣  እያለ የሚጨምር ነው፤ ከእርሻ የሚገኘው ምርት ደግሞ የእድገቱ መጠን አያጥፍም፤ 1፣ 2፣ 3፣ 4፣ 5፣ 6፣ 7፣ 8፣ 9፣ 10፣ እያለ የሚሄድ ነው፤  የመምሬ ማልቱስን ሀሳብ በሌላ መንገድ ካየነው የበላተኞች ቁጥር እያጠፈ ሲያድግ የምግቡ አቅርቦት የሚያድገው ግን በጣም በዝግተኛ ፍጥነት ነው፤ የሚል ነው፤  እንግዲህ የሕዝብ ቁጥርና የምርት አቅርቦት እኩል መጓዝ ሲገባቸው የሕዝቡ ቁጥር እየቀደመ ስለሚገኝ፣ መምሬ ማልቱስ የደረሰበት መደምደሚያ የሕዝቡን ቁጥር ለመቀነስ በሰው ልጆች መሀከል በሽታ፣ ችጋርና ጦርነት የማይቀሩ ይሆናሉ፤ ችጋር፣ ጦርነትና ሌሎችም አደጋዎች በሕዝቦች ላይ እየደረሱ የሕዝብ ቁጥርና የምርት እድገት በሚያደርጉት መሽቀዳደም መሀከል ሚዛንን ይጠብቃሉ።
መምሬ ማልቱስ በነበረበት ዘመን ላይ ሆኖ ከሃምሳና መቶ ዓመታት በኋላ እውቀትና (ሳይንስ) የእውቀት ጥበብ የሚያስከትሉትን መሠረታዊ የአስተሳሰብ፣ የአሠራርና የኑሮ ለውጥ ለመገንዘብ አልቻለም፤ እንዴት ብሎ? በመምሬ ማልቱስ ዘመን በአንድ ሄክታር መሬት ላይ የሚገኘው ምርት አምስት ኩንታል ብቻ ቢሆን በኋላ ግን በአንድ ሄክታር ላይ በእውቀትና በእውቀት ጥበብ ኃይል ምርቱን ከእጥፍም በላይ ማምረት የሚቻልበት ዘመን መጣ፤ ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያ፣ የተለያዩ የእርሻ ዘዴዎች የእርሻውን ሥራ ቀልጣፋና ምርታማ አደረጉት፤ በዚህም ምክንያት የመምሬ ማልቱስን ሀሳብ ብዙ ሰዎች ይነቅፉት ጀመር፤ ሆኖም የመምሬ ማልቱስን ሀሳብ ዛሬም ቢሆን ሙሉ በሙሉ ጊዜ አልሻረውም፡፡

Thursday, October 3, 2013

ድሆችን ያፈናቀለው “ኢንቨስትመንት” ዕዳ ዋጠው

"እኛን የሚያሳስበን በሊዝ ያልሸጥነው መሬት ነው" መለስ

DSCN0291


“መሬታችንን ለምን እንነጠቃለን?” በማለት የጠየቁ ተገድለዋል። ተገርፈዋል። ታስረዋል። አሁን ድረስ እስር ላይ የሚገኙ አሉ። ባዕድ እንኳን ባልሞከረው የከፋ ጭካኔ በከባድ መሳሪያ በተደገፈ የጦር ሃይል የተወለዱበትን መሬት እንዲለቁ የተገደዱ አዛውንቶች ላይ የተፈጸመው ግፍ እስከ ወዲያኛው የሚያሽር አይደለም። በሌሊት እርቃናቸውን ከሚያርፉበት ታዛ ስር ነፍጠኛ ሰራዊት እንዲከባቸው እየተደረገ የተፈጸመው አስነዋሪ ግፍ ጊዜ የሚጠብቅ እንደሆነ በየጊዜው የሚገለጽ ነው።
“የዘራሁትን ሳላነሳ በዶዘር ማሳዬን ጠረጉት፣ በዶዘር እርሻዬ ውስጥ ገብተው አረሱት፣ መሬቴን ለምን ትወስዳላችሁ? የት ልትወስዱኝ ነው? ያሸተውን በቆሎዬን መነጠሩት። ምን ላደርግ እችላለሁ። መሳሪያ የያዙ ወታደሮች ከበውኛል፣ ጠዋት ስነሳ ማሳዬ ባዶ ሆኖ አገኘሁት … ” ይህ ሁሉ የበደል ሰቆቃ ነው። በምስል ተደግፎ የቀረበ ህሊናን የሚሰብር መረጃዎች አሉ።

ከ130 በላይ የጀልባ ስደተኞች ኅልፈተ-ሕይወት

የአደጋ ደራሽ ሰራተኞች ካገኙት 82 አስክሪን መካከል በርካታ ሴቶች እና ሁለት ህጻናት ይገኙበታል። እንደ ከተማዋ ከንቲባ የጀልባዋ ተሳፋሪዎች ዛሪ ማለዳ በጀልባዋ ዋ ላይ ሳሉ እሳት ከተነሳ በኋላ፤ ለብዙ ሰዓታት ባህሩ ዉስጥ ነበሩ።አብዛኞቹ ተሳፋሪዎች ከኤርትራ እና ከሶማልያ እንደሆኑ ፖሊስ ተናግሯል።

አንዲት 500 ያህል ሰዎችን የጫነች ጀልባ በጣልያን የባህር ጠረፍ አካባቢ በደረሰባት የእሳት አደጋ ሰበብ ቢያንስ የ133 ሰዎች ህይወት ጠፋ ፤ 200 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት አልታወቀም ። ከአደጋው የ151 ሰዎች ህይወት ማትረፍ ተችሏል ። Ansa የተሰኘዉ የጣልያን የዜና አገልግሎት የላምፔዱዛን የባህር ወደብ ከተማ ከንቲባ፤ ጉይቺ ኒኮሊኒን ጠቅሶ ዛሪ እንደዘገበዉ፤ የአደጋ ደራሽ ሰራተኞች ካገኙት 82 አስክሪን መካከል በርካታ ሴቶች እና ሁለት ህጻናት ይገኙበታል። እንደ ከተማዋ ከንቲባ የጀልባዋ ተሳፋሪዎች ዛሪ ማለዳ በጀልባዋ ዋ ላይ ሳሉ እሳት ከተነሳ በኋላ፤ ለብዙ ሰዓታት ባህሩ ዉስጥ ነበሩ። ከአደጋዉ የተረፉት ግለሰቦችም ከፍተኛ ድንጋጤ ዉስጥ ይገኛሉ። የጣልያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤንሪኮ ሌታ ክስተቱን « ከባድ አደጋ » ብለዉታል። የጣልያን ምክር ቤት አባል ካሊድ ቹኪ አደጋዉን እንደሰሙ እንዲህ ነበር ያሉት