Monday, May 19, 2014

ከዞን-9 ታሣሪዎች ስድስቱ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ፖሊስ በሽብር አድራጎት እጠረጥራቸዋለሁ ብሏል፤ ፍርድ ቤት የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የፊደል ቁመት 
መለስካቸው አምሃ
 —   
የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/

ላለፉት 23 ቀናት ክሥ ሳይመሠረትባቸው ታስረው ከሚገኙት ዘጠኝ የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ሚድያ ፀሐፊዎች የሆኑ ጋዜጠኞችና አምደኞች ስድስቱ ዛሬ፤ ቅዳሜ፣ ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት የጋዜጠኞቹንና የአምደኞቹን ጉዳይ ያየው በዝግ ሲሆን የቀረቡት ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋዓለም ወልደየስ እና ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ሌሎች ሦስት አምደኞች መሆናቸው ታውቋል፡፡
  
የዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡየዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡ
ዛሬ ችሎት ያልቀረቡት አምደኞች መቼ እንደሚቀርቡ ለጊዜው በትክክል ባይታወቅም ሰሞኑን ይቀርባሉ የሚል ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡

Thursday, May 15, 2014

እምዬ ምኒልክ ሲመጥቅ፣ ወያኔ ሲወድቅ


May 15, 2014
ከሮበሌ አባቢያ፤ 14/5/2014
ቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ
ወያኔ በ1983 አዲስ አበባ ሲገባ እግረ መንገዱን የገበሬውን ልጆች፣ ጋዳፊና የአረብ ሀገር ከበርቴዎች ባስታጠቁት ዘመናዊ ታንክና መሣሪያዎች፣ እያጨደ በሬሳቸውና በደማቸው ላይ እየተረማመደ እንደነበር መሪር የቅርብ ትዝታ ነው። በቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ ይመራ የነበረው ጎጠኛው የወያኔ መንግሥት፣ የኢጣልያ ፋሺስት ያወጣውን በተለይ በአማራና በኦሮሞ ላይ ያነጣጠረውን የከፋፈለህ ግዛው ፖሊሲ ኮርጆ በመከተል፣ የአፄ ምኒልክ ሐውልት እንዲፈርስ ለማደረግ ሕዘቡን አነሳስቶ እንደነበር ይታወቃል።ሆኖም ሙከራው ወያኔ አስቦት በነበረበት ወቅት ባይሳካም፣ ሐውልቱን የማንሳት ሃሳብ አሁንም አለ። ስለዚህ ሕወሐት የሚመራው በውስጡ በሚስጥር በተሰገሰጉ ባንዳዎች እንደሆነ እያደር ሊታወቅ ስለቻለ የእምዬ ምኒልክ ወደጆች መዘናጋት የለባቸውም።
Ethiopian king Atse Menelik
ሐውልቱና ከኢጣልያን ጋር የተደረጉት ሁለት ከባድ ጦርነቶች
እምዬ ምኒልክ፣ እስከ አፍንጫው ድረስ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ በገፍ ታጥቆ ኢትዮጵያን ሊወር የመጣውን ጦር፣ አድዋ ላይ ገጥመው ወራሪውን ድባቅ መትተው አንፀባራቂ ድል ሲጎናፀፉ፣ ከሰሜን ሸዋ አብሮአቸው የዘመተው ስምንት ሺህ (8000) ፈረሰኛ የኦሮሞ ሚሊሽያ ሠራዊት በጦርነቱ ለተገኘው ድል ወሳኝ አስተዋፅዖ አድርጎ እንደነበረ በታሪክ የተመዘገበ የጀግንነት ሐቅ ነው። የአድዋው ድል የአውሮፓን ሀያላን መንግሥታትን አስደንግጦ ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሉአላዊ ነፃ ሀገር እንዲያውቋት አስገድዷቸዋል። ይህ ታላቅ የጥቁር ሕዝብ ድል በዓለማችን ላይ ለሚገኙት ጭቁን ጥቁሮች ሁሉ ሕያው ተስፋ ሰጥቷል።
በሽንፈቷ ሀፍረት የተከናነበችው ኢጣልያ፣ 40 ዓመት ሙሉ በሚስጢር ስትዘጋጅ ቆይታ፦ ሀ) በሚሊሽያዎቻችን ላይ ከሰማይ በአውሮፕላን የቦምብ ናዳ በማዝነብና በዓለም ሕግ የተከለከለውን መርዝ በመርጨት፤ ለ) በምድር በታንክና በመትረየስ የታገዘ መጠነ ሠፊ የሰለጠነ እግረኛ ጦር በማዝመት፤ ሐ) ሕዝቡን በጎሳ ከፋፍላ እርስ በርሱ በማጫረስ፤ መ) አማሮችና ኦሮሞዎች የሥልጣኔ ተፃራሪዎች ስለሆኑ ሌሎች ጎሳዎች በጠላትነት እንዲፈርጇቸው በመስበክ፣ አዲስ አበባን (ሸገርን) እንደ አውሮፓ ዘመን አቆጣጠር በ1936 ዓ.ም ለመቆጣጠር ችላለች። ዋቢ፦ Habešská Odyssea (YeHabesha Jebdu) የሃበሻ ጀብዱ by Adolf Parlesak Translated by Techane Jobre Mekonnen
የፋሺስትን ወረራ ያልተቀበሉት የኢትዮጵያ አርበኞች (በአዲስ አባባና በአካባቢው የሚገኙትን ኦሮሞዎችን ጨምሮ)፣ አራዳ ጊዮርጊስ በዳግማዊ ምኒልክ ሐውልት ዙሪያ ማታ ማታ እየተሰበሰቡ (ሬዲዮ አድማጭ መስለው) ይመካከሩ ነበር። ግራዚያኒ ይህን ሲሰማ ሐውልቱ እንዲነሳና በምሥጢር እንዲቀበር አዘዘ፤ በትእዛዙም መሠረት ሐውልቱ ተነስቶ ሌላ ጋ ተቀበረ። ፋሽስት ኢጣልያ ተሸንፎ ከሀገራችን ሲባረር፣ ሐውልቱ ከተቀበረበት ቦታ ተመልሶ እንደገና በቀድሞ ቦታው ላይ ሊተከል ቻለ።
ጠላት ተገዶ ያከበራቸውን እምዬ ምኒልክን ማክበር የምንኮራበት መብታችን ነው። እምዬ ምኒልክ ሲልቅ፣ የባንዳዎች ውላጅ ወያኔ ሲበሽቅ ሁሌ እደሰታለሁ። ምኒልክ አንድ ያደረጋትን ኢትዮጵያን ወያኔ ሲበታትናት አበክረን መቃወም የውዴታ ግዴታችን ነው። በዚህ ጉዳይ ለሚቃወሙን ተቺዎች መልሳችን ይሄው ነው።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር
አፄ ምኒልክ ከአንኮበር ወደ ሸገር ሲመጡ ያጋጠማቸው ተፋላሚ ቱፋ ሙና የተባለ ሐይለኛ የኦሮሞ ገዢ ነበር። አፄው ብልሀተኛ ስለነበሩ አማላጅ ልከው ታረቁና ቱፋ ሙናን ክርስትና አንስተው አበልጅ ሆኑ። የቱፋ ሙና ሰፊ ዘሮች እነ አቶ ብሩ ጎሮንቶ ገፈርሳ ግድብ አካባቢ በስተ ምዕራብ-ደቡብ አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ይኖሩ ነበር። አቶ ብሩን ባጋጣሚ ሱሉልታ አግኝቻቸው ከተዋወቅን በሗላ፣ ከባለቤቴ ጋር ገፈርሳ ድረስ እየሄድን እንጠይቃቸው ነበር። አቶ ብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ በተገኘበት በታላቅ ሥነሥርዓት ገፈርሳ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በተፈፀመው ቀብራቸውም ላይ ተገኝቻለሁ።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር (አዲሰ አበባ) የመጡት በኦሮሞ ባላባቶች የሚታዳደሩትን ግዛቶች አቋርጠው ነው። ቱፋ ሙና ብቻ ነው በነውጥ የተፋለማቸውና ውጊያው በእርቅ የቆመው። በነገራችን ላይ፣ የ1966ቱ አብዮት ሲፈነዳ እኔ አሰከማቀው ድረስ በሸዋ ውስጥ ሰፍኖ የቆየው ባላባታዊ ሥርዓት አራማጆች በአብዛኛው አለጥርጥር የኦሮሞ ተወላጆች ነበሩ።
የተወለድኩት አዲሰ አበባ ቀጨኔ ጋላ ሰፈር በሚባላው መንደር ውስጥ ነው። የከተማውን ዙሪያ ደህና አድርጌ አውቃለሁ። ሸዋ ውስጥ በልጅነቴ በእግሬና በፈረስ ከዚያም ስጎረምስ በመኪና በብዙ አቅጣጫዎች ተዘዋውሪያለሁ። ለምሳሌ፣ ከአዲስ አበባ ተነስተን እስከ 130 ኪሎሜትር ርቀት ዙሪያውን በወፍ በረር ብንቃኝ፣ የክልሉን ባላባትነት የአንበሳውን ድርሻ የኦሮሞ ተወላጆች ይዘውት እንደነበር አያከራክርም ለማለት ይቻላል። አፄ ምኒልክ የመሬት ግብር አስከፈሉ እንጂ የባላባቶችን የመሬት ይዞታ አለምክንያት አልነኩም። ዘውዱንም መሬቱንም እኔ ይዤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ሊቀረው ነው ብለው የመሬት ባለቤትነት በግል የእያንዳንዱ ዜጋ ይዞታ መሆን እንዳለበት በችሎት ላይ ስለመፍረዳቸው በአድናቆት ይነገርላቸዋል።

Monday, May 5, 2014

TPLF/EPRDF’s Divisive and Polarizing Political Master Plan is the Problem: Addis Ababa Master Plan is simply the Symptom


May 5, 2014
by Alem Mamo
The suffocatingly oppressive political rule of TPLF/EPRDF has continued to terrorize the people of Ethiopia, denying them their basic human rights to live in peace, dignity, and inclusive harmony. Since coming to power in 1991, the TPLF-led regime has implemented a deliberate system of permanent polarization and suspicion between and among communities. Obviously, the objective of this policy of permanent polarization and compartmentalized order is to weaken the ability of the Ethiopian people to resist and defeat this brutal totalitarian regime.
Addis Ababa Master Plan
The genesis and history of TPLF/EPRDF is deeply tied with its addiction to violence, murder, torture, and mass terrorization. The events of the last two weeks in Addis Ababa, Ambo, and other parts of the country are a clear testament of TPLF/EPRDF’s violent nature and it’s disregard for the sanctity and dignity of human life. First, there was the arrest of nine Zone 9 bloggers for no other reason than reporting and speaking truth to power. These young members of Zone 9 are representatives of their generation, committed to taking their rightful place in history. They knew all too well that the regime’s intolerance and even disdain for press freedom could make them a prime target. However, these young budding journalists/bloggers continued to inform the public and expose the crimes of the regime to the world, even if it meant going to jail and facing all physical and psychological suffering that comes with imprisonment. Their arrest has reaffirmed the fact of the TPLF/EPRDF regime’s unflinching commitment to keeping the people of Ethiopia under its clenched fist, and their fear of what Zone 9 bloggers/journalists are doing to report and resist. As the bloggers/journalists have articulated, there are two types of prisons in Ethiopia: the notorious Makalawi (which is divided into 8 zones) and prison dungeons spread all across the county; and the open-air prison which is the entire country (and where the name Zone 9 comes from). The bravery of these young bloggers/journalists is a profound lesson to all who fight for democracy, freedom, and justice, and their message is clear – freedom is not free!

Monday, April 28, 2014

ሠማያዊ ፓርቲ የነፃነት ትግልና የሃበሻ ጀብዱ

April 28, 2014

ዳኛቸው ቢያድግልኝ
በቅርቡ የሴቶችን ቀን አስመልክቶ በተደረገ የሩጫ ዝግጅት ወቅት የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችነ ነን ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች “አትለያዩን! አትከፋፍሉን! ነፃነት እንሻለን! ለድሃው ይታሰብለት! ኑሮ ከበደን! ውሃ ጠማን! መብራት ናፈቀን!” በማለት በጣም ሰብዓዊና እናታዊ ጥሪ ጮክ ብለው አሰምተው ነበር። ይህም መልካም ድርጊታቸው ለፍትህና ለአንድነት የሚደረግ ህዝባዊ ጥሪ በሚያስበርግጋቸው የወያኔ ባለስልጣናት ሁከት ፈጠራ ተብሎ ተወነጀሉ። ፕሮፌሰር አልማርያም በተቆጣው ብዕራቸው

… ያገሬ ወይዛዝርቶች በምህረት አልባ ጨካኞች ሲንገላቱና ሲወገሩ ከዳር ቆሜ ማየትን ህሊናዬ ፈጽሞ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም የእንግልታቸው ምክንያት ሰብዓዊ በሆነው መብታቸው ድምፃቸውን ስላሰሙ በመሆኑ የነሱና የመሰሎቻቸውን ጥሪ በዚህም ሳቢያ የሚደርስባቸውን አበሳ ሁሉ ለአለም አሳውቅ ዘንድ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ…

Semayawi party, ye habesha jebdu

ብለው ነበር። ከርሳቸው ድምጽ ጋር በማበር የሚያስተጋቡ ድምጾች ይኖሩ ዘንድ እውነት ነውና የኔንም ድርሻ እነሆ እጮሃለሁ። ጩሀቴም ቀደም ሲል በግፍ ለታጎሩ የህሊና እስረኞችና ሰሞኑን ለታፈሱት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና ደጋፊዎች አንዲሁም ለጎበዞቹ የዞን ዘጠኝ የሕዝብ አፈቀላጤዎችም (ብሎገሮችም) ነጻነት ያለኝ ጽኑ ፍላጎት መገለጫ ነው።
ሁከት ማለት የሌሎችን ሰላም ማደፍረስ፥ አምባጓሮና ጸብ ማንሳትና ማነሳሳት፥ የንብረት ጥፋትና በሰዎች ላይ አካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳትን ማስከተል ነው። እኒህ ወጣት ሴቶች ግን ከዚህ በተቃራኒው የተንገላቱት ሰላም አንዳይደፈርስና ህዝብ እንዳይጎዳ በስልጣን ላይ ያሉት መንግስታዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሰላማዊ ጥሪ ነበር ያቀረቡት። የሀሰት ፕሮፖጋንዳው ሰለባ ያልሆነ በሙሉ ወጣቶቹ በአንድነትና በፍትህ የጸናች ሀገር ለመረከብ ከዚህ የበለጠ ቢያደርጉም ተገቢ ነው የሚል ይመስለኛል። የነርሱ አሳሪዎች በነርሱ እድሜ ጠመንጃ አንስተው መጥፎ ነው ብለው የፈረጁትን መንግስት ለመዋጋት ጫካ መግባታቸውን አለመርሳት ብቻ ሳይሆን እንደትልቅ ገድል በየመድረኩና በየመጽሀፉ ሲናገሩና ሲያስነግሩ እንሰማለን። ታዲያ የዛሬው ትውልድ ያውም እንደነሱ ሰው ለመግደል ጠብመንጃ ሳያነሱ ፍትህ አይጉዋደል ብለው በሰላም መጠየቃቸው እንዴት መጥፎ ሁኖ ነው ለእስርና እንግልት የሚዳርጋቸው? ማሰርንና አፈናን እንደ የስልጣን ዘመን ማራዘሚያ አማራጭ አድርጎ መውሰድ ከሚያስብ አእምሮ ሳይሆን በፍርሃት ከተዋጠና ለውጥ አይቀሬ መሆኑን መቀበል ካቃተው ደካማ ጭንቅላት የሚመጣ ነው። በአንጻሩም ነገ የነርሱ የሆነው ወጣቶች በፍርሀት ተገንዘው አረመኔዎች ሀገራቸውንና ተስፋቸውን ሲያጠፉባቸው በዝምታ ሊያዩ አይቻላቸውም።

Ethiopia should immediately release bloggers (HRW)

April 28, 2014

Human Rights Watch
(Nairobi) – The Ethiopian authorities should immediately release six bloggers and three journalists arrested on April 25 and 26, 2014, unless credible charges are promptly brought.
Human Rights Watch on Ethiopia
United States Secretary of State John Kerry, who is scheduled to visit Ethiopia beginning April 29, should urge Ethiopian officials to unconditionally release all activists and journalists who have been arbitrarily detained or convicted in unfair trials. The arrests also came days before Ethiopia is scheduled to have its human rights record assessed at the United Nations Human Rights Council’s universal periodic review in Geneva on May 6.
“The nine arrests signal, once again, that anyone who criticizes the Ethiopian government will be silenced,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “The timing of the arrests – just days before the US secretary of state’s visit – speaks volumes about Ethiopia’s disregard for free speech.”
On the afternoon of April 25, police in uniform and civilian clothes conducted what appeared to be a coordinated operation of near-simultaneous arrests. Six members of a group known as the “Zone9” bloggers – Befekadu Hailu, Atnaf Berahane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Zelalem Kibret, and Abel Wabela – were arrested at their offices and in the streets. Tesfalem Weldeyes, a freelance journalist, was also arrested during the operation. Edom Kassaye, a second freelance journalist, was arrested on either April 25 or 26; the circumstances of her arrest are unclear but all eight individuals were apparently taken to Maekelawi Police Station, the federal detention center in Addis Ababa, the capital.

Wednesday, April 23, 2014

የወያኔዎች አስቂኝ መመሪያዎችና ዐዋጆች


April 23, 2014
ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)
በመጀመሪያ የክርስትና እምነት ተከታይ አንባቢዎች እንኳን ለ2006ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
ሕወሓት ወደ ሥልጣን መጥቶ በዓይነቱ የተለዬ የጥቁር አፓርታይድ ሥርዓትን በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ካቆመ ወዲህ እጅግ ብዙና ለመቁጠርም የሚያዳግቱ መመሪያዎችንና ዐዋጆችን ቀርፆአል፡፡ አንዳንዶቹን በዘፈቀደና በነሲብ እየቸከቸከ በፈለገው ሰዓትና ወቅት ራሱ ተግባራዊ በማድረግ፣ አንዳንዶቹንም ለማስመሰል ያህል በእንቅልፋምና ደናቁርት የ“ፓርላማ” አባላቱ አማካይነት በዐይን ጥቅሻ በሚታዘዝ የሆዳም ማይማን ጭብጨባ “አጸድቆ” ሥራ ላይ በማዋል ሀገርንና ሕዝብን ማተራመስ ከያዘ ሁለት ዐሠርት ዓመታትን ጨርሶ የሦስተኛውን ዐሠርት አንድ ሦስተኛ ያህል ጊዜ ለማገባደድ ጥቂት ወራት ብቻ ይቀሩታል፡፡
ከቅርቦች ልጀምር፡፡ ቅድም ቡና ስጠጣ እንዲህ የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡ እውነት ይሁን ሀሰት ገና አላረጋገጥሁም – ይሁን እንጂ የወያኔን ባሕርይ ለሚያውቅ ይህን ወሬ ሀሰት ነው ማለት የሚያስችል አዲስ ነገር አይገኝም፡፡ ከዚህ የበላለጡ አስቂኝና አስገራሚ መመሪያና ዐዋጆችን እየታዘብን 23 የመከራና ፍዳ ዓመታትን ስላቀናን ይህኛውን የተለዬ አያደርገውም፡፡ የሰማሁት ምን መሰላችሁ – ልማታዊ የወያኔ ሙዚቀኞችና ዳንኪረኞች በኮፒራይት መቸገራቸውን ስላመለከቱና ለዚህም ችግር መባባስ ትልቁን ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት የስልኮች ሚሞሪዎችና ብሉቱዝ በመሆናቸው እነዚህን አገልግሎቶች የሚሰጡ ማናቸውም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ መንግሥት ማገጃ አውጥቷል የሚል ነው፡፡ በዚህም ሳቢያ የእጅ ስልኮችና የመሳሰሉት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ማዕቀብ ሊጣልባቸው እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡ ለነገሩ ከኢትዮጵያ የወያኔ ሚዲያዎች በውዴታየ ስለራቅሁ ይህ መመሪያ በገሃድ ወጥቶ ይሁን አይሁን እስካሁን አላወቅሁም፡፡ በበዓሉ ምክንያት ከጎረቤት ውጪ ራቅ ወደሚል ሌላ ውጪ አልወጣሁም፡፡ ግን አይሆንም አይባልም፡፡ ወያኔ ከፈለገ “ከዛሬ ጀምሮ ከትግሬ በስተቀር ነጭ ጤፍ እንጀራ የሚበላና ጮማ የሚቆርጥ ሌላ የማኅበረሰብ ክፍል እንዳይኖር ዐውጃለሁ፤ ቢኖር ግን ህገ መንግሥቱን በኃይል ለመናድ እንደቃጣ ተቆጥሮ በአሸባሪነት የክስ ቻርጅ እስከሞት ሊደርስ በሚችል ከፍተኛ ቅጣት ዋጋውን ያገኛል፡፡” ብሎ ሊያውጅ ይችላል፡፡ ማንን ወንድ ብሎ ነው ወያኔ የፈለገውን ከማድረግ የሚቆጠበው? ወያኔ በምን ይዳኛል? በምንም፡፡ ለነገሩ ቀን የሰጠው ጅብ አንበሣንና ነብርን ሲቆረጣጥም ቢታይ ዘመኑ የትንግርት ነውና አያስገርምም፡፡ በኢትዮጵያም ሆነ በተቀረው ዓለም እየሆነ ያለውም ይሄውና ይሄው ብቻ ነው፡፡ ግን ግን በሀገራችን ለወደፊቱ ጅብ የማያሸንፍበትን ቀዳዳ መዝጋት የሚያስችለንን ታላቅ የሦስተኛው ሚሌንየም ሥልት መንደፍ እንደሚገባን ከወያኔው አዋራጅ የተፈጥሮ ልክስክስ ጠባይ የተማርን ይመስለኛል፤ የመንጌን አማርኛ ልጠቀምና ብታምኑም ባታምኑም የአፄውና የደርጉ ሥርዓቶች መንገዱን ባበጃጁለት ወያኔ ክፉኛ ተዋርደናል፡፡ አሸንፎ የማያውቅ ትንሽ ሰው እንዳያሸንፋችሁና መሣቂያና መሣለቂያ እንዳያደርጋችሁ በርትታችሁ ጸልዩ፡፡ ትንሽ ስል ማሸነፍን እንደህልም ይቆጥር የነበረ የባንዳዎችና የሥነ ልቦና ደዌ የተጣባቸው በበቀልና ጥላቻም የተሞሉ ዜጎች ውላጅ የሆኑ መለስን፣ ስብሃትንና ሣሞራን የመሰሉ የታሪክ አራሙቻዎች ማለቴ ነው፡፡ እንደነዚህ ያሉ ቀላሎች በታሪካዊ መደላድሎች መመቻቸት ምክንያት አንዳች ዕድል ካገኙ እንዴቱን ያህል ወጥ እንደሚረግጡና ነገሮችን በምን ያህል ደረጃ እንደሚያበለሻሹ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ለማንኛውም ሚሞሪ ያላቸው ስልኮችና መሰል ጋጄቶች ሊከለከሉ ነው አሉ፡፡ አልጋህ ውስጥ ተደብቀህም በሙዚቃ መቆዘም ሊቀር ነው፡፡ ኧረ ባል በሚስቱና ሚስትም በባሏ ቀረጥ እንዳይከፍሉ ያሰጋል፡፡ “እያንዳንድሽ ማን በሚገዛው ሀገር ውስጥ ተኝተሸ ዓለምሽን ትቀጫለሽ?” ብሎ ምቀኛው ወያኔ ለአንድ ግንኙነት ብር 50 ግብር ቢጥልና በየጉያችን ኤሌክትሮኒክ ሥውር ባልቦላ(ማይክሮቺብስ) እንደኖር ፕላንት ቢተክል ባለትዳሮች ምን ይውጠናል? ያቺው ብቸኛ መዝናኛችን ላይ ወያኔ በመብረቃዊ የማጥቃት እርምጃው ቢዘምትባት ወዴትና ለማንስ አቤት እንላለን? የሰይጣን ጆሮ ይደፈን፡፡ የምንተነፍሰውን አየርና የፀሐዩንማ በኑሮ ውድነቱ ላይ ጨምሮ ባልተወለደ አንጀት እያስገፈገፈን ነው፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተላለፈ ጥሪ!


April 23, 2014
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ለመሆኗ አለም ይመሰክርላታል፡፡ አንቱ የተባሉ ምሁራንን በማፍራት ለዓለም አበርክታለች፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአለም ካሉ ታላላቅ ዩንቨርስቲዎች እና የምርምር ተቋማት እስከ አመራነት ድረስ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መገኘታቸው ነው፡፡ እነዚህ ምሁራን በተሰማሩበት ስራ መስክ የሚያስመዘግቡት ውጤት እና በስራቸው ተሸላሚ መሆን ላነሳነው ሀሳብ ማጠናከሪያነት ያገለግለናል፡፡ እጅግ የሚያሳዝነውና ልብ የሚሰብረው ግን ሀገራችን ከእነዚህ ውድ ልጆቿ ተገቢውን ዋጋ አለማግኘቷ ነው፡፡ ሀገራችን የወላድ መካን እየሆነች ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሆነ ተብሎ የሚቀነባበር ሴራ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ብትሆንም ቅሉ በተከታታይ ስልጣኑን የጨበጡት ጭፍን አንባገነኖች በሚያራምዱት አግላይ ምሁር ፖሊሲ ምክንያት እውቀታችሁን እና ገንዘባችሁን በምትወዷት ሀገራችሁ ኢንቨስት አድታደርጉ ሁኔታዎች ባለመመቻቸታቸው የስደትን መራራ ጽዋ እንድትጨልጡ ተገዳችኋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተለይ ባለፉት 10 አመታት በተቃዋሚዎች መዳከም የሚያታግል ኃይል አጥታችሁ እንደቆያችሁም እናምናለን፡፡
ፓርቲያችን ሰማያዊ እያንዳንዱ ዲያስፖራ ሀገር ቤት ያለውን ዜጋ ያክል የኢትዮጵያዊነት መብት አለው ብሎ ያምናል፡፡ ይህ ይረጋገጥ ዘንድም አጥብቆ ይታገላል፡፡ በተለያየ ሁኔታና ወቅት አንባገነኖችን በሀገር ውስጥ እንደታገላችሁ እናምናለን፡፡ ለዚህ ትግላችሁና ለከፈላችሁት ዋጋም እውቅና እንሰጣለን፡፡ በስርዓቶቹ ጨካኝ ዱላ እና ሰቆቃ ብዛት ውድ ሀገራችሁን ትታችሁ የሥደትን ኑሮ ትገፉ ዘንድ ቢበየንባችሁም ስለ ኢትዮጵያ ከመብሰልሰል እንዳልዳናችሁና ሀሳባችሁ ሀገር ቤት ስለ መሆኑ መስካሪ አያሻም፡፡

ህወሓት እስከመቼ ደም ማፍሰሱን ይቀጥላል ? (አቶ ሀብታሙ አያሌው UDJ)


April 23, 2014
ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ…………… ‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡
Ato Habtamu Ayalew (UDJ)
አልገባኝም ….ቀጠልኩ ….የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? መለሰ …..እኔ ምን ላድርግ ? …..የከለከለው ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? አዎ አጭር መልስ፡፡ ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡ ‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም›› ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤ አልወሰድንም የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡

Thursday, April 17, 2014

Ethiopians in Norway discussed the current political situation in Ethiopia and the role of the Diaspora


April 16, 2014
This meeting was organized by the Democratic Change in Ethiopia Support Organization in Norway (DCESON) and took place on the 12th of April 2014 in Oslo from 15.00-21:00 p.m.
The meeting attended by around 200 Ethiopians who live in Oslo and the other parts of Norway.
It was attended by around 200 Ethiopians who live in Oslo and the other parts of Norway. The guest speaker at the meeting was ato Bizuneh Tsige who is the member of the leadership of Ginbo7 movement for justice, democracy and freedom. The guest speaker held a broad speech.
The public meeting was opened by holding a minute of silence to remember the victims of the TPLF racist rulers and prisoners of conscience in Ethiopia. The minute of silence was led by ato Abi Amare who is in charge of the public relations part of the DCESON. Following this, ato Yohannes Alemu, the chairman of the DCESON spoke about how the DCESON was established and its objectives. He told the participants that the organization at the moment supports the UDJ party that is based in Ethiopia and Ginbot7 that is based in exile (abroad). Moreover, he stressed that all Ethiopians should overcome their differences and contribute to the decisive all sided struggle to get rid of the racist rule of the TPLF in Ethiopia.


April 17, 2014
ሰማያዊ ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉምዝ በህገ ወጥ መንገድ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ቦታቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱና ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ባካሄዳቸው ሰላማዊ ሰልፎችና ባወጣቸው መግለጫዎች የጠየቀ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው ምላሽ ባለመስጠቱ ዜጎቹ የተፈናቀሉበትን ቡለን ወረዳና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ላይ ክስ መስርቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ክሱን ታዋቂው የዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማሪያም ይዘውት የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ቢሮክራሲያዊ ምክንያቶች መዝገብ ሳይከፈትለት እንደቆየ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡
Amhara Ethnic group members Ethiopia
ይሁን እንጂ ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገው ተደጋጋሚ ግፊት ክሱ በአሁኑ ወቅት መዝገብ ተከፍቶለት፣ የዳኝነት ክፍያ ተከፍሎ በቀጣይ ሀሙስ ሚያዝያ 9/2006ዓ/ም ክሱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃብሄር ችሎት ላይ መታየት እንደሚጀምር ኃላፊው ገልጸዋል፡፡
‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በጉዳዩ ላይ አቋም ወስዶበት ከሰላማዊ ሰልፉም ባሻገር ዜጎቹ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና ካሳ እንዲሰጣቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ እስካሁንም ድረስ በዜጎች ላይ በሚደርሰው ችግር ከጎናቸው ሆኖ የሞራልና የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡›› ያሉት አቶ ብርሃኑ ፓርቲው ኢትዮጵያውያኑ በመፈናቀሉ ሂደት በደረሰባቸው ችግር ልጆቻቸው የታመሙባቸውን ለህክምና እንዲሁም ለመጓጓዣም ፓርቲው እገዛ ሲያደርግ መቆየቱንና አሁንም ዜጎቹ ፍትህ እስኪያገኙ ድረስ ከጎናቸው እንደሚሆኑ አሳውቀዋል፡፡

Tuesday, April 15, 2014

“ዘላለማዊነት ለገንዳዎች!! ዘላለማዊ ክብር ለገንዳዎች”

የድህነት ራዳር እንደ ድህነት "ክፉ" ነው

hailemariam qurt


የገንዳዎች የደራጃ መዳቢ ድርጅት ሊቋቋም ይገባል። ገንዳዎች የኑሮ መሰረት የሆኑላቸው እየበረከቱ ስለሆነ በደረጃ መከፋፈል አለባቸው። የአጠቃቀማቸውም መመሪያም በግልጽ ሊቀመጥ ይገባል። የደረጃዎች መዳቢ ድርጅት ቢያንስ በገንዳዎች ውስጥ ስለሚጣሉ ቆሻሻዎች መመሪያ በማውጣት የሚበሉ ነገሮች ከሌሎች አይነት ቆሻሻዎች ተለይተው እንዲጣሉ ማዘዝ አለበት። ከሸራተንና ከቤተ መንግስት የሚወጡ የምግብ ትራፊዎች ተጠቃሚ ጋር ሳይደርሱ ፓስተር እንዲመረመሩ የሚያዝ መመሪያ ቢወጣም መልካም ነው። ቀጭኑ ዘ-ቄራ ማሳሰቢያ አለው።
ገንዳዎች የኢህአዴግን ስራና ሃላፊነት በመወጣት ለድህነት ሰለባዎች “የላቀ” አስተዋጽኦ እያበረከቱ ስለሆነ የሽልማት ኮሚቴ ይቋቋምላቸው። ገንዳዎች በሚወጣላቸው ደረጃ መሰረት ተለይተው ይሸለሙ። የጥሬ ስጋ ተጠቃሚዎችና አንዳንድ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሽልማቱን ለግል ውዳሴ እንዳይጠቀሙበት አቶ ደመቀ መኮንን የሚመሩት ተቆጣጣሪ ይመደብ። ይህ የእለቱ ጥቆማዬ ነው። ገንዳዎች ባይኖሩ ኖሮ ምን ይኮን ነበር? “ዘላለማዊነት ለገንዳዎች!! ዘላለማዊ ክብር ለገንዳዎች!!”

በኖርዌ ያሉ ኢትዮዽያውያን የወያኔን የስለላ መረብ በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

April 14, 2014

Ethiopians demonstration in Norway
በ11-4-2014 በኖርዌ ያሉ ኢትዮዽያውያን የወያኔን የስለላ መረብና ኖርዌ በስደተኛው ላይ ያላትን ፖሊሲ በመቃወም    የተቃውሞ ሰልፍ አረጉ።  23 ዓመት እራሱ መራጭ እራሱ ተመራጭ ሆኖ በጠመንጃ አፈሙዝ ህዝቡን እያንቀጠቀጠ የኖረው ወያኔ አንድ ቀን ሕዝብ በቃኝ ብሎ አንቅሮ እንደሚተፋውና ንብ ሆኖ ለነፃነቱ እንደሚነሳ ማወቅ ነበረበት።

የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ


April 14, 2014
የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ
Ginbot7 meeting in Norway
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ  የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014  በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ  የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን  የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::
ሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 15:00 እስከ ምሽቱ 21:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ በኢትዮጵያ ውስጥ በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ  በዚሁ ዘረኛ ቡድን አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን  የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::
በመቀጠለም አቶ ዮሀንስ አለሙ የዴምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር የመግቢያ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸው ስለ ዲምክራሲያዌ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አመሰራረት እና ስለ ድጋፍ ድርጅቱ አላማ በማብራራት የድጋፍ ድርጅቱ በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤት በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት ለመጣል እየታገሉ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶችን እየረዳ እንደሚገኝ እና ከሀገር ውጭ ደግሞ የወያኔን መንግስት  በሁለገብ ትግል  ለማስወገድ እየሰራ ያለውን የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሴ ንቅናቄ የፖለቲካ ድርጅትን በግንባር ቀደምነት እየረዳ እንዳለ በመግለጽ  የወያኔን ዘረኛ ስርአት ለመጣል ሁሉም ሰው አስተዋጿ ማድረግ እንደሚጠበቅበት እና ማንኛውም  ኢትዮጵያዌ ዜጋ በሀገራችን የጋራ ጉዳይ ስለሆነው  የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ሀሳብ በመለዋወጥ ፣በመካከላችን ያሉትን ማንኛውንም የሃሳብ ልዩነቶች ወደ ኋላ በመጣል ፣ በመቻቻል፣ ሀገር እያፈረሰ እና ሕዝብ እያዋረደ ያለውን የዘረኛውን የወያኔን መንግስት ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሁለገብ ትግል ለማስወገድ መረባረብ እንዳለበት አጽኖት ሰጥተው ንግግር አድርገዋል::
Ethiopians public meeting in Norway
በመቀጠለም ዲምክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ድጋፍ ከሚሰጣቸው ድርጅቶች መካከል አንዱ የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል የሆኑት አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ ሰፊውን ጊዜ በመውሰድ ከንጉሱ ስርአት ጀምሮ በደርግ መንግስት ዘመንም በሀገራችን የተደረጉ የፖለቲካ ንቅናቄዎችንና ለውጦችን አንድ በአንድ በመዘርዘር አሁን ካለው የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ጋር በማነጻጸር ሰፋ ያለ ትንታኔ ያቀረቡ ሲሆን አሁን ላይ ሀገሪቱን እየመራው ነው የሚለው የወያኔ መንግስት ከዚህ ቀድሞ ኢትዮጵያን ከመሩት ከሁለቱ መንግስታቶች ማለትም ከንጉሱም ከደርግም መንግስት ጋር ሲነጻጸር ፈጽሞ እንደማይገናኝ የወያኔ መንግስት ዘረኛና የዘረኝነት ፖለቲካ እያራመደ ያለ አረመናዊ መንግስት እንደሆነ አብራርተዋል::

Tuesday, April 8, 2014

እኛና አብዮቱ፤ በፍቅረሥላሴ ወግደረስ፣ ፀሐይ አሣታሚና አከፋፈይ፣ታህሣሥ 2006 ዓ ም፤ ግምገማ በታደለ መኩሪያ


April 8, 2014
በታደለ መኩሪያ
ደራሲው መጽሐፉን ለምን ለመጻፍ እንደተነሳሱ በመግቢያው ላይ ገልጸዋል፤ በከፍተኛ የሥልጣን እርከን ላይ ተካፋይ የሆኑበት የደርግ መንግሥት የሚገባውን የታሪክ ሥፍራ አልተሰጠውም፤ ስለደርግም የጻፉ ቢኖሩም ፣ ለመጪው ትውልድ ትክክለኛውን የታሪክ ሐቅ አላስጨበጡትም  ባይ ናቸው።
Former Ethiopian official Fikreselasie Wegderes new book
መጽሐፉን አንብቤዋለሁ፤ 440 ገጾች አሉት፤ኩነቶች ባይደጋግሙ በ200 ገጽ ሊያጥር ይችላል፤ ደራሴው በተለያዩ የሥልጣን እረከኖች ሠርተዋል፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን በቅተዋል፤ ከግል ማኅደራቸው ተነስተው  ይህቺን ጥንታዊ ሀገርና ሕዝቧን   ለአሥራ አምስት ዓመት ‘እኛ’ ከሚሏቸው ጓዶቻቸው ጋራ እንዴት  እንደመሯት ከዚያም ያገኙትን ተመክሮ ለትውልድ የሚያስተላልፉበት አጋጣሚ አግኝተዋል፤ የኔ ጥያቄ አጋጣሚውን ‘እኛና አብዮቱ’ በሚለው መጽሐፋቸው ተጠቅመውበታል ወይ ነው? ይህን በጋራ የምናየው ይሆናል። ለአንድ ወታደር ስለጦር ሜዳ ውሎ  ቢጽፍ ይብልጥ  ውጤታዊ ይሆናል፤ በተግባር ተካፍሏልና። ደራሴው በነፃ አስተሳሰብ ተኮትኩተው ባላደጉበት፣ ሕብረተሰቡም በነፃነት ሐሣቡን በማይገልጽበት፤ በሕዝብ ስም ሀገር የሚመሩትም ለዜጎች ግልጽ ባልሆኑበት፣ትክክለኛ ታሪክ ጽፎ ለትውልድ ማስተላለፍ ይቻላል ወይ? የሚለውን ጥያቄ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ግን ትክክለኛ ነው ያሉትን ታሪክ  በተረጋገጠ እውነት ላይ መሥርተው ካለቀረቡት የታሪክነት ደረጃውን አጥቶ ተረት ተረት ይሆናል።  ከሁሉ በላይ ደግሞ የጸሐፊው እውነትን በተረጋገጠ እውነት ለማቅረብ  ያለው የስዕብና ጥንካሬ  ወሳኝ ነው።
ስለ ስዕብናን ካነሣሁ ዘንዳ ‘የሕይወቴ ታሪክ’ የፊታውራሪ ተክለሃውሪያት ተክለማሪያም የሕይወት ታሪክ መጽሐፍ ነው፤ ከዚህ መጽሐፍ ያገኙሁት ቁምነገር ጀባ ብያችሁ ወደ ግምገማዬ አመራለሁ፤ ፊታውራሪ ተክለሃውሪያት በልጅነታቸው ራስ መኮንንን ተከትለው አደዋ ዘምተዋል፤ አጎታቸውን በጦርነቱ ላይ አተዋል፤ ከጦርነቱ በኋላ ራስ መኮንንን አስፈቅደው ወደማያውቁት አገር ሶቪየት ሕብረት ሄደው በታወቀ የጦር ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ሀገር ተመልሰዋል። የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር በመሆን ሲሰሩ በዙ የአልጋ ወራሽ ተፈሪ መኮንን ግብር በላዎች ሊያሰሯቸው አልቻሉም። አልጋ ወራሹም እንደሌሎቹ ሎሌያቸው እንዲሆኑ ጠየቋቸው። የሀገራቸውን ነፃነት ተክብሮ እንዲኖር ለመታደግ ስለጦርነትና የጦር መሣሪያ ያጠኑት ፊታውራሪ ተክለሃዋሪያት ተክለማሪያም ሎሌነትን ተጠየፉት፤ የእርሶ ሎሌ አልሆንም አሏቸው፤ በአልጋ ወራሹ ሥር የሚያሽቃብጡ ግብር በላዎች የሆነ ያልሆነውን እያስወሩባቸው፣በእግር ብረት ታሰሩ፣ከቤተሰባቸው ተነጠሉ፣ በቤተመንግሥት እንደለማኝ ፍርፋሪ ተጣለላቸው፤ ግን ቅንጣት ታክል ስዕብናቸውን ዝቅ አላደረጉትም፤ የኢትዮጵያዊነት ስዕብና! የእኛነታችን አሸራ! የታላቅ ሙሑር ተመስሌት፣ የመጪው ትውልድ አብነት እንበላቸው።

MEDREK or the End of a Political Masquerade?


April 8, 2014
Messay Kebede is Professor of Philosophy at the University of Dayton.
Messay Kebede
It is now abundantly clear that the project of creating a strong multiparty opposition by uniting unitary parties and ethnic parties is anything but feasible. The inability of MEDREK to achieve unity despite numerous attempts as well as Dr. Negaso Gidada’s––who stepped down from the chairmanship of the strongest unitary party, namely, UDJ––recent convoluted declaration in which he said, “I oppose secession but support the right to secession,” seal the definitive collapse of the project. The sticking point, if one can decipher it in the maze of attacks and counterattacks, is the irreconcilable position of ethnic and unitary parties on the right to self-determination up to secession of the various ethnic groups composing Ethiopia. Another sticking point deriving from the right to self-determination is that parties have no right to campaign for political support or vote in regions that they do not represent ethnically. While the right to self-determination up to secession keeps Ethiopian unity in life support, the implication that regions are reserved for ethnic politics only does no more than remove the very purpose of unitary parties. Under these conditions, it is no surprise if the project of unity could not but fail completely.

Wednesday, April 2, 2014

ፋሲል የኔዓለምን የምተችበት ምክንያት አገኘሁ!

April 2, 2014

‹‹መሬት ተሸጠ አልተሸጠ›› ኢህአዴግ መደገፍን ምን አመጣው?

ከጌታቸው ሺፈራው
ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ሰሞኑን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ፡፡ መሬት አይሸጥም፤ አይለወጥም›› የሚል ጽሁፍ አስነብቦናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስርዓቱን የሚተቹ ወይንም የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት ምክንያት አገኘሁ›› ማለት ይቅርና ትችታቸው የሰላ ሆኖ ካልተገኘ ‹‹ወያኔ›› መባላቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ፋሲል ይህንን የፖለቲካ ባህላችን እያወቀና ደፍሮ ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ!›› ማለቱ በራሱ ይበል የሚያሰኝ አዲስ ባህል ነው፡፡
Land grab in Ethiopia
በእርግጥ ፋሲል ኢህአዴግን እደግፈዋለሁ ሲል በጭፍን አይደለም፡፡ ከግራ ፖለቲካው የተቀነጨበ ‹‹ካፒታሊስቶች መሬቱን ተቆጣጥረው አርሶ አደሩን መሬት አልባ ያደርጉታል፡፡›› የሚል መከራከሪያ አንስቷል፡፡ ይህ መከራከሪያ በዚህ ዘመን ደግሞም ፋሲል እደግፈዋለሁ ያለው ኢህአደግ ራሱም ሆነ በቅርቡ የሚገኙት ባለሃብቶች መሬትን በተቆጣጠሩበት በአሁኑ ወቅት ባይሆን ኖሮ ‹‹ለአቅመ መከራከሪያነት›› ብቁ በሆነ ነበር፡፡
‹‹መደገፍን ምን አመጣው?››
ፋሲል በአሁኑ ወቅት መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ በተወሰኑ የስርዓቱ ደጋፊ ካፒታሊስቶች እንደሚያዝ ሲፈራ ስርዓቱ በመሬት ጉዳይም ብልሹ መሆኑን እየገለጸልን ነው፡፡ ታዲያ የዚህ ብልሹ ስርዓት ተግባራዊ የማትሆን አንዲት ዘለላ ‹‹መርሁ›› እንዴት ትደገፋለች? ኢህአዴግ መሬትን አይሸጥም አይለወጥም የሚለው አርሶ አደሩን ጨምድዶ ለመያዝ እንደሆነ ፋሲልን መምከር የሚቻል አይደለም፡፡ በዚህ መንገድ ኢህአዴግ ዘመናዊ ጭሰኛ መፍጠሩ መቼም ቢሆን ድጋፍ ሊያስገኝለት አይችልም፡፡
በሌላ መልኩ የፋሲል መደገፊያ ምክንያትም ቢሆን በአሁኑ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነው፡፡ ፋሲል መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ ካፒታሊስቶች መሬት ስለሚያካብቱ የአርሶ አደሩ መሬት በጥቂት ግለሰቦች እጅ ይወድቃል ይለናል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የጥቂቶች መንግስት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መሬት የ‹‹መንግስት ነው!›› ሲባል ህወሓት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ ውጭ ‹‹መንግስት›› በሚባለው መዋቅር እያገለገለ ነው ሊለን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወረቀት ላይ ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም›› ተብሎም ቢሆን መላው የአገሪቱ መሬት ጥቂቶቹ ገዥዎች እንደፈገሉ የሚጠቀሙበት ከመሆን አልዳነም፡፡

[በአባይ ግድብ ዙሪያ የተጻፈ አጭር ሀተታ] ትንሹዋ ወያኔና ትልቁ ወያኔ አላኖሩኝም

April 2, 2014

ነፃነት ዘለቀ (አዲስ አበባ) 
ለለውጥ ያህል ከራሴ ችግር ብጀምር ምን አለበት? ግለሰብ ካልኖረ ማኅበረስብ አይኖርም፡፡ ደሞም የኔ ችግር የሁሉም ፣ የሁሉም ችግር የኔ መሆኑን የማያምን አንባቢ ቢኖር ችግር አለበት ማለት ነውና በጊዜ ራሱን ፈትሾ መድሓኒት ቢጤ ቢያፈላልግ ሳይሻለው አይቀርም፡፡
TPLF is just like a Rat
ትንሹዋ ወያኔ ጠምሳኛለች፡፡ እኔን ብቻም አይደለም የጠመሰችው፡፡ ብዙዎች ኢትዮጵያውያንንም እንጂ ነው፡፡ ከወያኔ ባልተናነሰ ሁኔታ ኑሯችንን እያቃወሰችው ትገኛለች – ትልቁ ወያኔ በደጅና በቤት ውስጥ እርሷ ደግሞ በቤት ውስጥ ብቻ በተናጠልና በቡድን እየተጋገዙ ወዲያ ወዲህ ውልፊት ልንል በማይቻለን ሁኔታ ወጥረውናል፡፡ ምን እንደምናደርግም ጨንቆናአለ፡፡ ይቺ የቤት ውስጥ ወያኔ ዐይጥ ናት፡፡
ዘመኑ ለይቶለት የዐይጦችና  የወያኔዎች ሆኗል ወንድሞቼና እህቶቼ ማለትም ኢትዮጵያውያን፡፡ በኔ ቤት የተረፋት ነገር የለም፤ ለወትሮው ካልሲና ጨርቃ ጨርቅ እየለቃቀመች ነበር ወደጎሬዋ እምትወስድ፡፡ ዛሬ ግን ዘመን ተቀይሮ ባዶ ሞሰብ ሣይቀር መቆርጠም፣ አልሙኒየም የምጣድ አከንባሎ መጎርደም፣ ቁም ሣጥን መቀርጠፍ ይዛለች፤ ወያኔነት ከዚህ በላይ አለ? መጽሐፎችን አንብባ ላታነብ ነገር በጥርሶቿ መከታተፍ፣ ምግቦችን ከጉሮሮዋችን እየነጠቀች ማንከት፣ በሌሊትና አንዳንዴ ደግሞ በማንአለብኝነትና ወደር በሌለው ዕብሪት በቀንም ቤትን ተቆጣጥራ ሰላምን ማወክ የዘመናችን ትንሹዋ ወያኔ ገደቡን ያለፈ የድፍረት ተግባር ሊሆን በቅቷል – ወያኔን ተማምና መሆን አለበት መቼም፡፡ ድፍረቷ እኮ ድፍረት እንዳይመስላችሁ፡፡ ኧረረረረረ…. እንዳቃጠልሽኝ የሚያቃጥል ይዘዝብሽ፡፡ ብዙ ሰዎች በርሷ እንደተቸገሩና ዘመኑ ለርሷና ለወያኔ ዓይነቶቹ ምሥጥ መሠሪዎች የሰጠ መሆኑን ይህን ችግር የማወያያቸው ሰዎች ሁሉ ይነግሩኛል፡፡
ዛሬና አሁን በኢትዮጵያ የሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 6፡30 ገደማ ሲሆን ቀን የገዛሁትን እንትን በስምንት የጦር ግምባር አጥምጄ ወደብሶት አደባባይ መውጣቴ ነው – እንዳትሰማኝና እንዳታውቅብኝ ነው የገዛሁትን ነገር በእንትን የገለጸኩላችሁ ታዲያን – እንጂ “እዚያው በላች እዚያው ቀረች” የሚል አደገኛ መርዝ መግዛቴን ለመናገር አፍሬ እንዳይመስላችሁ፡፡ ለነገሩ ወያኔና ዐይጥ ከጠላታቸው የሚከላከሉበት ብዙ ተለዋዋጭ ዘዴ ስላላቸው በበሶ ዱዔት ያዘጋጀሁትን ግብዣ እንደሚቀበሉትና እንደማይቀበሉት አላውቅም – ውጤቱን ነገ አያለሁ፤ ዲዲቲና ወባ እንኳን ተለማምደው ጓደኛሞች መሆናቸውን ቀደም ሲል ሰምተን የለም? የሆነው ሆኖ ችግሩ ቀላል እንዳይመስላችሁ፤ ከአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት የተለቀቁ ነው የሚመስሉት – እንደደፋርነታቸውና እንደሆዳምነታቸው፡፡ የሚምሩት ነገር እኮ የላቸውም፡፡ የሚሆንልኝ መስሎኝ “ዕቃ አትንኩብኝ፤ ቤቱ እንደሆነ ይበቃናል፡፡ ካለኝ አልፎ አልፎ ቀለብ እቆርጥላችኋለሁ – ከሌለኝ ግን ምን አደርጋለሁ? ብቻ አትተናኮሉኝ እንጂ እኔ መርዝ አላጠምድባችሁም፤ የዛሬን ኑሮ መቼም እናንተም ታውቁታላችሁ፡፡ ከመጠለቁ እግርን የሚፋጀው እሳተ መለኮቱ የቻይና ካልሲ እንኳን ባቅሙ ሠላሣና ዐርባ ብር በገባበት ወቅት እባካችሁን ተከባብረን እንኑር፡፡…” ብዬ ቃል ገብቼ በቤቴ ውስጥ የሚያደርሱትን ጉዳት ሰምቼ እንዳልሰማሁና ዐይቼም እንዳላየሁ ለብዙ ጊዜ ትቻቸው ነበር፡፡ እነሱ ግን የእንጀራ ሞሰብ አልጋችን ላይ አስቀምጠን ከባለቤቴ ጋር በየተራ እየጠበቅን እስክናድር ድረስ አሰቃዩን – የቤት ውስጥ ወያኔዎች! አሁን ባሰብኝና ቃሌን አፈረስኩ፡፡ እናም … የነሱስ አብነቱ ቀላል ነው፡፡ አለ እንጂ ወያኔ ለያዥ ለገራዥ ያስቸገረ! የወያኔስ ሰማያዊ መርዝ ካልተጨመረበት በምድራዊ መርዝ ብቻ አይጠራም፡፡ እናም ጎበዝ ግዴላችሁም ለላይኛውም በርትተን እንጩህ፡፡ የቃመ ብቻ ሣይሆን የጮኸም ተጠቀመ ሲባል ሰምቻለሁ፡፡
ወያኔና ዐይጥ አንድ ናቸው፡፡ ይሉኝታ አያውቁ፤ ፍቅር አያውቁ፤ ሀፍረትና ኅሊና እሚባል የላቸው፤ የተረገሙ ፀረ-ሕዝቦች፡፡
የሰሞኑ የወያኔ ኢቲቪ ወሬ የአባይ የህዳሴ ግድብ ብቻ ሆኗል፡፡ ነገሩ “አንድ ያላት እንቅልፍ የላት” ዓይነት ነው፡፡ በሌሎች ሀገራት በየአሥር ኪሎ ሜትሩ የሚገኝ ግድብ ኢትዮጵያ ውስጥ ብርቅ ሆኖ ጆሯችን እስኪደነቁርና እጅ እጅ እስኪለን ድረስ አባይን እየተጋትን ነው፡፡ ይህ ግድብ ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታው ይልቅ ፖለቲካዊ ፋይዳው እንደሚያመዝን ቀድሞውንም የታወቀ ነው፡፡ ፈረንጆቹ አንድን ነገር “politicized” ሆኗል ሲሉ ያ እንዲያ ሆነ የሚሉት ነገር በፊት ለፊት ከቆመለትና ከሚወራለት ዓላማ ውጪ ለሌላ ጉዳይ ውሏል ማለታቸው ነው፡፡ የወያኔ የህዳሴ ግድብም ወያኔ እንደሚለው ለሀገሪቱ የሚሰጠው የተለዬ ጥቅም ኖሮ ሣይሆን ሕዝብን ለማዘናጊያነትና ሊጠቀስም ሣይጠቀስ ሊዘለልም ለሚችል የተለዬ ፖለቲካዊ ፍጆታ መሆኑን እናውቃለን፡፡ አለበለዚያ የስድስት ሺህ ሜጋ ዋት ኮረንቲ ከቁም ነገር ተጥፎ እስከዚህን ድረስ 24 ሰዓት ከበሮ የሚያስደልቅና ይቀምሰውና ይልሰው ያጣን ድሃ ሕዝብ ያለ ርህራሄ የሚያዘርፍ ሆኖ አይደለም፡፡ “አንቺ ቁም ነገርሽ የጎመን ወጥሽ” እንደምንል ወያኔም በዚህች ድልድይ ማነው ግድብ ዕንቅልፍ አጥቶ እኛንም እንደሱ አትተኙብኝ እያለን ነው፡፡

ህግን ተላልፈን ከህገወጦች ጋር አንተባበርም! (ከአንድነት የአዲስ አበባ ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ)

April 2, 2014
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

ከአንድነት የአዲስ አበባ ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ
Andenat Party UDJ
የእሪታ ቀን በሚል መሪቃል በመዲናችን አዲስ አበባ ያሉ ማህበራዊና ኢኮ ኖሚያዉ ቀውሶችን አስመልክቶ በተለይም ከተማዋን ወደ ማህበራዊ ቀውስ እየመሯት የሆኑትን የውሃ፣ መብራት፣ ስልክ፣ የትራንስፖርት ችግር እንዲቀረፍ ህዝቡ የተቃውሞ ድምፁን እንዲያሰማ መጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ለማካሄድ ያቀደውን ሕዝባዊ ሠላማዊ ሠልፍ አስመልክቶ በህዝብ መገናኛ ብዙሃን ይፋ ካደረግንበት ቀን ጀምሮ የሚጠበቅብንን ህጋዊ የማሣወቅ ሥራዎችን ስንሠራ የቆየን መሆኑና መድረስ ለሚገባው አካል ሁሉ አካል ሁሉ በተገቢው ሁኔታ ማሳወቃችን ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ጥሪው ለሕዝብ ይፋ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ የሚመለከተው የሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል በህግ የተቋቋመበትን ኃላፊነት በመዘንጋት ለጠየቅነው ጥያቄ ቀጥተኛ መልስ ከመስጠት ይልቅ ህግ በመተላለፍ ክልከላ አዘል ደብዳበ ልኳል፡፡ ሆኖም የአንድነት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት በትላንትናው እለት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ለሠላማዊ ሠልፍ ማሳወቂያ ክፍል የላከው ደብዳቤ በአዋጅ ከተደነገገ ህግ ጋር የሚጣረስና የዜጎችን መብት የሚያፍን መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የአንድነት ምክር ቤት ግንዛቤ በመያዝ ከዚህ የሚከተለውን የአቋም መግለጫ በማውጣት ለመገናኛ ብዙሃን እንዲተላለፍ ወስኗል፡፡
የአቋም መግለጫው የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር የሠላማዊ ሠልፍና የፖለቲካ ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ፓርቲያችን መጋቢት 15 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ላስገባለት የሠላማዊ ሠልፍ እውቅና መጠየቂያ ደብዳቤ መጋቢት 17 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በሠጠው ምላሽ የሠላማዊ ሠልፍ ጥያቄውን አለመቀበሉን ማሳታወቁንና ለዚህ ደብዳቤ የላክንለትን መልስ አልቀበልም በማለት የወጣ ነው፡፡

Tuesday, March 25, 2014

Who is who in the Ethiopian Ministry of Foreign Affairs?


March 24, 2014
Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs (Tigre)
Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs (Tigre)
by Muse Abebe
Despite the claim of TPLF that the federal system has equally protected the rights of ‘nations and nationalities’, the political and economic power is fundamentally controlled by Tigayans who use the cultural differences in the country to their divide and rule strategy.  In the past, Ghinbot 7 and Esat Television were exposing the Tigrean monopoly of almost all positions in the Ministry of Defence, security apparatus and foreign diplomatic missions. Exposing the people who are in control of real power in the country helps to increase the awareness of the public about the nature of the apartheid like regime in Ethiopia. Ghnbot 7 and Esat as well as other democratic organizations need to continue working on this important issue. One of the federal 

የግብጽ ፍርድቤት 530 በሚሆኑ የሙስሊም ወንድማማች አባላት ላይ ሞት ፈረደ

ተከሳሾቹ ለአንድ ፖሊስ ኃላፊ መሞት ተጠያቂዎች ናቸው
egypt 5


* ውሳኔው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል
በሕዝብ ከተመረጡ በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተወገዱትን የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲን በመደገፍ በፖሊስ ጣቢያ ላይ አደጋ አድርሰው የነበሩ 529 ተጠርጣሪዎች ትላንት ሰኞ ዕለት የሞት ቅጣት ተበየነባቸው፡፡ የብይኑ ፍጥነትና የተፈረደባቸው ተከሳሾች ብዛት አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከሆነ ውሳኔው ለይግባኝ የሚቀርብ ሲሆን በሙስሊም ወንድማማች ላይ ሆን ተብሎ የተነጣጠረ ጥቃት እንደሆነ ዘግቧል፡፡
egypt 3በዓለማችን በቅርብ ጊዜያት ከተካሄዱ የሞት ፍርድ ብያኔዎች በብዛትም ሆነ በፍጥነት ለየት ያለ እንደሆነ የተጠቀሰለት ይህ የፍርድ ሂደት በግብጽ የሕግ የበላይነት እየከሰመ የሄደ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ በርካታ የሕግ ምሁራን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተከሳሾቹ በሙሉ የሙስሊም ወንድማማች አባላትና የቀድሞው ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ደጋፊ መሆናቸው ብያኔው እውነተኛ የፍርድ ሂደት የተከተለ ሳይሆን ወደፊት ሊነሳ ለሚችል ተቃውሞ ማስተማሪያ እንዲሆን ታቅዶ የተከናወነ ነው ሲል የፍትሕ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ አሶሺየትድ ፕሬስ በተጨማሪ ዘግቧል፡፡
ተከሳሾቹ የቀረበባቸው ክስ ባለፈው ነሐሴ ወር ሚኒያ በተባለች የግብጽ ከተማ በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በተከናወነ የነፍስ ግድያ፣ የግድያ ሙከራ፣ መንግሥትን ለመገልበጥ ሕገወጥ ቡድንን መቀላቀል እና የመንግሥትን የጦር መሣሪያ መስረቅ በሚሉ ወንጀሎች ናቸው፡፡ በወቅቱ በፖሊስ ጣቢያው ላይ በደረሰ ጥቃት የሚኒያ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ሞሐመድ አል-አታር መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጥቃት በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዘው ወታደራዊው አገዛዝ በሙስሊም ወንድማማች ደጋፊና አባላት ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነና አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ በዚያን ወቅት ብቻ ከ600 በላይ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል፡፡
ከ545 ተከሳሾች ውስጥ 528ቱ ጥፋተኞች ሆነው በመገኘታቸው የሞት ፍርድ እንደተበየነባቸው የመንግሥት ሚዲያ ሲያስታውቅ አንዳንድ ባለሥልጣናት ቁጥሩ 529 እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 150 በሌሉበት ፍርዱ የተበየነባቸው ሲሆን የተቀሩት ግን በነጻ ተለቅቀዋል፡፡ በግድያው የተሳተፉት ብቻ ፍርድ ሊበየንባቸው ይገባል በማለት የሚከራከሩ ወገኖች እንደሚሉት በማስረጃነት የቀረቡት 20 የሚሆኑ የቪዲዮ ምስሎች እንደሚያሳዩት የተወሰኑ ሰዎች የፖሊስ አዛዡን በብረት በትር ሲደበድቡ እና አንድ ሐኪም ደግሞ በእሣት ማጥፊያ የኦክስጂን ሲሊንደር (ካንስተር) የፖሊሱ ጭንቅላት ሲፈረክስ ታይቷል ይላሉ፡፡

Monday, March 24, 2014

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ


ግልጽነትና ተጠያቂነት ፈረዱ ወይስ ተፈረደባቸው?
short eiti eprdf


ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።

Ethiopian Regime Detained Opposition Party Leader, Terrorized Semayawi Party Members


March 24, 2014
Mr. Yilkal Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party
Mr. Yilkal Getnet
Ethiopian American Council (EAC)
Silver Spring, Maryland, March 23 – Just before boarding time last Friday night, airport personnel told Mr. Yilkal Getnet that he was to report to a Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF) officer at Bole Airport, Addis Ababa, Ethiopia. Mr. Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party, was leaving Ethiopia to attend a Young African Leaders Initiative (YALI) fellowship program in the United States.
Mr. Getnet’s luggage was removed from the plane and he had to endure three hours of intense questioning by some TPLF so-called “security agents” which caused him to miss his flight. Mr. Getnet, educated as a civil engineer, returned to his home around 2 a.m. Saturday morning.

Wednesday, March 19, 2014

የሃይማኖት እርጅና አያድርስ


March 19, 2014
ይሄይስ አእምሮ
ይህችን ጽሑፍ ባልጽፋት በወደድኩ፡፡ ግን ያበጠው ይፈንዳ እንጂ እጽፋታለሁ፡፡ በስንቱ ታፍኜ እዘልቀዋለሁ? ብዙ ሚዲያዎች እንደማይቀበሉኝ ከወዲሁ አምናለሁ፤ በዚያ ብቻ ከማሩኝም እሰዬው ነው – ትልቅ ዕድለኝነት፡፡ እውነት በጠፋችባትና ሀሰት በነገሠችባት ዓለማችን ውስጥ ለሺዎች ዓመታት ዜጎችን እሥረኛና ባሪያ አድርጎ እግር ከወርች በማሠር ኮድኩዶ ያስቀረን ጉዳይ ድንገት ተነስቶ መተቸት በትንሹ ውግዘትን ማስከተሉ የሚጠበቅ ነው፡፡ And I am ready to welcome everything of anything.
በዓለም የሚገኙ ሃይማኖቶችን ብዛት ለመቃኘት ሞክሬ ያገኘሁት መልስ በጣም የሚለያይ ነው፡፡ አንዳንድ መረጃዎች የዓለም ዋና ዋና (ግንድ የሚባሉ) ሃይማኖቶችን ወደ 21 ሲያወርዷቸው አንዳንዶች ደግሞ ከአሥርና ከሃያ ሺዎች በላይ ያዘልቋቸዋል፡፡ አንድ ምንጭ ደግሞ 4200 አካባቢ እንደሚደርሱ ያትታል፡፡ የሆነ ሆኖ እንደመነሻዎቹ እንደአይሁድ እምነትም ይሁን እንደስንጣቂው የክርስትና እምነት ከዚያም ቀጥሎና ቆይቶ እንደመጣውም የእስልምና እምነት መሠረት የሰው ልጅ አጠቃላይ ብዛት ከሁለት ሰዎች ተነስቶ አሁን ወዳለበት ሰባት ቢሊዮን ገደማ እስኪደርስ ድረስ ከአንድ ወይም ከምንም ሃይማኖት ተነስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሃይማኖቶችን አሁን ሊከተል መቻሉ ሃይማኖትን ከመለኮታዊነት ይልቅ ይበልጡን ሰውኛ እንደሚያደርገው መገመት አይከብድም፡፡ ይህን ስል የሰው ልጅ ሃይማኖት ሊኖረው እንደሚገባ የማምን መሆኔን መግለጥ እወዳለሁ፡፡ የሃይማኖትን መብዛት ግን ከሰዎች ፍላጎት በዘለለ እግዚአብሔራዊ ነው የሚል የሞኝነት እምነት የለኝም፡፡ በመሆኑም በሃይማኖታዊ የአመስጥሮ ሥልት (mystification)  ሰዎች በሰዎች ሲታለሉና ጤናማ አእምሯቸውን በማስመሰያ ወጥመድ ሲሰለቡ ስመለከት አዝናለሁ ብቻ ሣይሆን ክፉኛ እበሳጫለሁ፡፡
እውነት አትመነዘርም፡፡ እውነት አትሸቀጥም፡፡ እውነት ምን ጊዜም መልኳን አትለውጥም፡፡ እውነት በሃይማኖት መለያየት ሰበብ አትከፋፈልም፤ ተከፋፍላም አራት ሺህና አሥር ሺህ እውነቶችን አትሆንም፡፡ ከዚህ አንጻር ታዲያ ይህ ሁሉ የሃይማኖት ልዩነት መንስኤ የሥጋ ፍላጎት እንጂ የነፍስ ፈቃድና የፈጣሪ ፍላጎት እንዳልሆነ መረዳት ይገባል፡፡