Tuesday, March 25, 2014

Who is who in the Ethiopian Ministry of Foreign Affairs?


March 24, 2014
Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs (Tigre)
Tewodros Adhanom, Minister of Foreign Afaairs (Tigre)
by Muse Abebe
Despite the claim of TPLF that the federal system has equally protected the rights of ‘nations and nationalities’, the political and economic power is fundamentally controlled by Tigayans who use the cultural differences in the country to their divide and rule strategy.  In the past, Ghinbot 7 and Esat Television were exposing the Tigrean monopoly of almost all positions in the Ministry of Defence, security apparatus and foreign diplomatic missions. Exposing the people who are in control of real power in the country helps to increase the awareness of the public about the nature of the apartheid like regime in Ethiopia. Ghnbot 7 and Esat as well as other democratic organizations need to continue working on this important issue. One of the federal 

የግብጽ ፍርድቤት 530 በሚሆኑ የሙስሊም ወንድማማች አባላት ላይ ሞት ፈረደ

ተከሳሾቹ ለአንድ ፖሊስ ኃላፊ መሞት ተጠያቂዎች ናቸው
egypt 5


* ውሳኔው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል
በሕዝብ ከተመረጡ በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተወገዱትን የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲን በመደገፍ በፖሊስ ጣቢያ ላይ አደጋ አድርሰው የነበሩ 529 ተጠርጣሪዎች ትላንት ሰኞ ዕለት የሞት ቅጣት ተበየነባቸው፡፡ የብይኑ ፍጥነትና የተፈረደባቸው ተከሳሾች ብዛት አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከሆነ ውሳኔው ለይግባኝ የሚቀርብ ሲሆን በሙስሊም ወንድማማች ላይ ሆን ተብሎ የተነጣጠረ ጥቃት እንደሆነ ዘግቧል፡፡
egypt 3በዓለማችን በቅርብ ጊዜያት ከተካሄዱ የሞት ፍርድ ብያኔዎች በብዛትም ሆነ በፍጥነት ለየት ያለ እንደሆነ የተጠቀሰለት ይህ የፍርድ ሂደት በግብጽ የሕግ የበላይነት እየከሰመ የሄደ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ በርካታ የሕግ ምሁራን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተከሳሾቹ በሙሉ የሙስሊም ወንድማማች አባላትና የቀድሞው ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ደጋፊ መሆናቸው ብያኔው እውነተኛ የፍርድ ሂደት የተከተለ ሳይሆን ወደፊት ሊነሳ ለሚችል ተቃውሞ ማስተማሪያ እንዲሆን ታቅዶ የተከናወነ ነው ሲል የፍትሕ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ አሶሺየትድ ፕሬስ በተጨማሪ ዘግቧል፡፡
ተከሳሾቹ የቀረበባቸው ክስ ባለፈው ነሐሴ ወር ሚኒያ በተባለች የግብጽ ከተማ በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በተከናወነ የነፍስ ግድያ፣ የግድያ ሙከራ፣ መንግሥትን ለመገልበጥ ሕገወጥ ቡድንን መቀላቀል እና የመንግሥትን የጦር መሣሪያ መስረቅ በሚሉ ወንጀሎች ናቸው፡፡ በወቅቱ በፖሊስ ጣቢያው ላይ በደረሰ ጥቃት የሚኒያ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ሞሐመድ አል-አታር መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጥቃት በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዘው ወታደራዊው አገዛዝ በሙስሊም ወንድማማች ደጋፊና አባላት ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነና አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ በዚያን ወቅት ብቻ ከ600 በላይ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል፡፡
ከ545 ተከሳሾች ውስጥ 528ቱ ጥፋተኞች ሆነው በመገኘታቸው የሞት ፍርድ እንደተበየነባቸው የመንግሥት ሚዲያ ሲያስታውቅ አንዳንድ ባለሥልጣናት ቁጥሩ 529 እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 150 በሌሉበት ፍርዱ የተበየነባቸው ሲሆን የተቀሩት ግን በነጻ ተለቅቀዋል፡፡ በግድያው የተሳተፉት ብቻ ፍርድ ሊበየንባቸው ይገባል በማለት የሚከራከሩ ወገኖች እንደሚሉት በማስረጃነት የቀረቡት 20 የሚሆኑ የቪዲዮ ምስሎች እንደሚያሳዩት የተወሰኑ ሰዎች የፖሊስ አዛዡን በብረት በትር ሲደበድቡ እና አንድ ሐኪም ደግሞ በእሣት ማጥፊያ የኦክስጂን ሲሊንደር (ካንስተር) የፖሊሱ ጭንቅላት ሲፈረክስ ታይቷል ይላሉ፡፡

Monday, March 24, 2014

ኢህአዴግ ባደባባይ የወደቀውን ፈተና “በጓሮ” አለፈ


ግልጽነትና ተጠያቂነት ፈረዱ ወይስ ተፈረደባቸው?
short eiti eprdf


ለግልጽነትና ለተጠያቂነት ብሎም ለህዝቦች ጥቅም ቅድሚያ እንደሚሰጥ ህግ ደንግጎ የተቋቋመው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ኢህአዴግ ያቀረበውን የይግባኝ ማመልከቻ ተቀብሎ ማጽደቁ አነጋጋሪ ሆኗል። በ2009 ኢህአዴግን “ያወጣሁትን መስፈርት አታሟላም” በማለት እውቅና የከለከለው ይህ ተቋም፣ ኢህአዴግ በሚከሰስባቸው ዋና ጉዳዮች ለውጥ ሳያደርግ የራሱን ውሳኔ የገለበጠበት አካሄድ እየተመረመረ እንደሆነ የጎልጉል ምንጮች ጠቁመዋል።
የኢህአዴግን የእውቅና ይግባኝ ጥያቄ ተቀብሎ ያጸደቀው የተፈጥሮ ሃብትን በትክክለኛ መንገድ ለሕዝብ ጥቅም መዋሉን በመከታተል ለአገራት እውቅና የሚሰጠው The Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) የሚባለው ዓለም ዓቀፋዊ ተቋም ነው። ተቋሙ ኢህአዴግ በ2009 አቅርቦት የነበረውን የእውቅና ጥያቄ ውድቅ ሲያደርግ የሰጠው ምክንያት “የመያዶች ህግ የተሰኘው” አዋጅ ተግባራዊ እንዳይሆንና በአገሪቱ የተተከሉት አፋኝ ህጎች እስካልተወገዱ ድረስ ማመልከቻው እንደማይታይ በማሳወቅ ነበር።
በ2009 ጠ/ሚኒስትር የነበሩት አቶ መለስ “መሰዋት” በስተቀር ኢህአዴግ አንዳችም ለውጥ ባላደረገበት ሁኔታ ባለፈው ረቡዕ መጋቢት 19፤2006 (March 19፤2014) ይኸው እውቅና ሰጪ ተቋም የራሱን ውሳኔ ቀልብሶ ለኢህአዴግ እውቅና መስጠቱ የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ከውሳኔው ቀናት በፊት በጓሮ የሚወጠን ድርጊት እንዳለ መረጃ ደርሶት የማሳሰቢያ ተቃውሞ ያሰራጨው ሂውማን ራይትስ ዎች የተሰኘውየሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት እንዳለው ከሆነ ከተገለበጠው ውሳኔ በስተጀርባ ሚስ ክሌር ሾርት ከፊት ረድፍ ተቀምጠዋል።

Ethiopian Regime Detained Opposition Party Leader, Terrorized Semayawi Party Members


March 24, 2014
Mr. Yilkal Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party
Mr. Yilkal Getnet
Ethiopian American Council (EAC)
Silver Spring, Maryland, March 23 – Just before boarding time last Friday night, airport personnel told Mr. Yilkal Getnet that he was to report to a Tigrayan Peoples Liberation Front (TPLF) officer at Bole Airport, Addis Ababa, Ethiopia. Mr. Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party, was leaving Ethiopia to attend a Young African Leaders Initiative (YALI) fellowship program in the United States.
Mr. Getnet’s luggage was removed from the plane and he had to endure three hours of intense questioning by some TPLF so-called “security agents” which caused him to miss his flight. Mr. Getnet, educated as a civil engineer, returned to his home around 2 a.m. Saturday morning.

Wednesday, March 19, 2014

የሃይማኖት እርጅና አያድርስ


March 19, 2014
ይሄይስ አእምሮ
ይህችን ጽሑፍ ባልጽፋት በወደድኩ፡፡ ግን ያበጠው ይፈንዳ እንጂ እጽፋታለሁ፡፡ በስንቱ ታፍኜ እዘልቀዋለሁ? ብዙ ሚዲያዎች እንደማይቀበሉኝ ከወዲሁ አምናለሁ፤ በዚያ ብቻ ከማሩኝም እሰዬው ነው – ትልቅ ዕድለኝነት፡፡ እውነት በጠፋችባትና ሀሰት በነገሠችባት ዓለማችን ውስጥ ለሺዎች ዓመታት ዜጎችን እሥረኛና ባሪያ አድርጎ እግር ከወርች በማሠር ኮድኩዶ ያስቀረን ጉዳይ ድንገት ተነስቶ መተቸት በትንሹ ውግዘትን ማስከተሉ የሚጠበቅ ነው፡፡ And I am ready to welcome everything of anything.
በዓለም የሚገኙ ሃይማኖቶችን ብዛት ለመቃኘት ሞክሬ ያገኘሁት መልስ በጣም የሚለያይ ነው፡፡ አንዳንድ መረጃዎች የዓለም ዋና ዋና (ግንድ የሚባሉ) ሃይማኖቶችን ወደ 21 ሲያወርዷቸው አንዳንዶች ደግሞ ከአሥርና ከሃያ ሺዎች በላይ ያዘልቋቸዋል፡፡ አንድ ምንጭ ደግሞ 4200 አካባቢ እንደሚደርሱ ያትታል፡፡ የሆነ ሆኖ እንደመነሻዎቹ እንደአይሁድ እምነትም ይሁን እንደስንጣቂው የክርስትና እምነት ከዚያም ቀጥሎና ቆይቶ እንደመጣውም የእስልምና እምነት መሠረት የሰው ልጅ አጠቃላይ ብዛት ከሁለት ሰዎች ተነስቶ አሁን ወዳለበት ሰባት ቢሊዮን ገደማ እስኪደርስ ድረስ ከአንድ ወይም ከምንም ሃይማኖት ተነስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ ሃይማኖቶችን አሁን ሊከተል መቻሉ ሃይማኖትን ከመለኮታዊነት ይልቅ ይበልጡን ሰውኛ እንደሚያደርገው መገመት አይከብድም፡፡ ይህን ስል የሰው ልጅ ሃይማኖት ሊኖረው እንደሚገባ የማምን መሆኔን መግለጥ እወዳለሁ፡፡ የሃይማኖትን መብዛት ግን ከሰዎች ፍላጎት በዘለለ እግዚአብሔራዊ ነው የሚል የሞኝነት እምነት የለኝም፡፡ በመሆኑም በሃይማኖታዊ የአመስጥሮ ሥልት (mystification)  ሰዎች በሰዎች ሲታለሉና ጤናማ አእምሯቸውን በማስመሰያ ወጥመድ ሲሰለቡ ስመለከት አዝናለሁ ብቻ ሣይሆን ክፉኛ እበሳጫለሁ፡፡
እውነት አትመነዘርም፡፡ እውነት አትሸቀጥም፡፡ እውነት ምን ጊዜም መልኳን አትለውጥም፡፡ እውነት በሃይማኖት መለያየት ሰበብ አትከፋፈልም፤ ተከፋፍላም አራት ሺህና አሥር ሺህ እውነቶችን አትሆንም፡፡ ከዚህ አንጻር ታዲያ ይህ ሁሉ የሃይማኖት ልዩነት መንስኤ የሥጋ ፍላጎት እንጂ የነፍስ ፈቃድና የፈጣሪ ፍላጎት እንዳልሆነ መረዳት ይገባል፡፡

መንግስት ስለ ጣይቱ ልጆች ጨንቆት ዋለ (Semayawi Party Update)


March 18, 2014
Semayawi Party- Ethiopia (Update)
ምንም የረባ መከራክሪያ ያላቀረበው ፖሊስ መናገር አቅቶት ሲንተባተብ ነው የዋለው በተጨማሪ ሌሎች መያዝ የልቻልናቸው 20 እሩጫው ላይ የነበሩ ሴቶች ስላሉ በማለት የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል ሲጀምር ችሎቱ የታየው በጽ/ቤት ነው የነበረው የሰዉ ብዛት ያስጨነቀው መንግስት ሰዉ በችሎት እንዳይታደም ክርክሩን እንዳይሰማ በጣም ጠባብ በሆነችው ቢሮ ከአቅሙዋ በላይ የሆኑ ተከሳሾችን ለማሰተናገድ ተገዳለች ውሳኔ መስጠት የማይችለው ዳኛ ለነገ መጋቢት 10/2006 በመደበኛ ይታይ በሚል ተልካሻ ምክንያት ቀጥሮአቸዋል የጣይቱ ልጆች ግን በጣም በሚያሰድሰት ሞራልና የትግለ ሰሜት ላይ ሆነው ለማየት ችለናል፡፡
ችሎቱንም ለመከታተል የተለያዩ ሀገራት የኢንባሲ ተወካዮች፤ የሰማያዊ ፓረቲ አባላትና ደጋፊዎች እነዲሁም ጋዜጠኞች ተገኝተዋል
እወነት ሁሌም ታሸንፋለች ሁሌም ከጎናችሁ ነን!!!

Sunday, March 16, 2014

Incarcerated Ethiopian journalist, Reeyot Alemu, spends 1000th day in prison


March 16, 2014
In a month when we are celebrating women, today, Sunday March 16th is Ethiopian journalist Reeyot Alemu’s 1000th day of imprisonment for simply doing her job.Ethiopian journalist Reeyot Alemu’s 1000th day of imprisonment
A columnist for several Amharic-language newspapers, Reeyot Alemu was one of the first journalists arrested in a 2011 government crackdown on dissent as authorities in Addis Ababa, unnerved by the Arab Spring revolutions, rounded up prominent journalists, intellectuals and political opponents and linked them to a vague terrorism plot.
While in pre-trial detention, she reported being pressured to sign a false confession to implicate co-defendants in imaginary crimes against the state.
Her refusal to cooperate earned her a sentence of 14 years in prison based on her newspaper columns in which she criticized the government’s record on corruption, its attacks on democracy and the rule of law, and the effects of repression on the population.
Her sentence was reduced to five years on appeal but she is pursuing an international appeal at the African Human Rights Commission.
Ms. Reeyot’s indomitable integrity and courage in defiance of the injustice of her imprisonment, has earned her international accolades such as the UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize, the International Women’s Media Foundation Courage in Journalism Award, and a finalist spot for the Sakharov Prize for Freedom of Thought.
She is among eight journalists imprisoned in Ethiopia, Africa’s second worst jailer of journalists after Eritrea.

“እኛና አብዮቱ” የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግ ደረስ ጸጸት አልባ ትዝታዎች


March 16, 2014
ከኤፍሬም የማነብርሐን
ሻምበል ፍቅረ ስላሴ ወግ ደረስ በጣም አስደናቂም አስገራሚም የሆነ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል። የደርግ አባልና ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ለአምባ ገነኑ ኮለኔል መንግስቱ ኃይለማርያም እንደቀኝ እጅ ባገለገሉበት ዘመን የሆነውን ሁሉ እሳችው ካመኑበት አቋም በመንደርደር ተርከውታል።  በጣም ብዛት ያላቸው የውስጥ ሰው ብቻ ሊያውቃቸው የሚችላቸው መረጃዎችን (ፋክትስ) መጽሐፉ አካቷል።  ብዙ ሰው ወደ ጀርባ ገፍቶት የነበረውን የዚያን የደም ዘመን ትዝታዎች እንደ አዲስ ይቀሰቅሳል።  ደራሲው መረጃዎችን በመሰብሰብና በተቀናጀ መልክ ታሪኩን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በማቅረባቸው ሊደነቁ ይገባል። ታሪክም ላቀረቡት ጽሑፍ እንደባለውለታ ያያቸዋል የሚል ግምት አለኝ።  የዚያ አስከፊና በኢትዮጵያ ላይ የማይሽር ጠባሳ ጥሎ ያለፈው የደርግ ቡድን አባል በመሆን ከድርጅቱ የተቆራኙ ቢሆኑም፣ ጽሑፉን በማዘጋጀታቸው ለአገር፣ ለወገን በአመዛኙ ጠቃሚ አስተዋጽኦ ለማቅረባቸው መጽሐፉ ቋሚ ምስክራቸው ይሆናል።
Former Ethiopian official Fikreselasie Wegderes new book
መጽሐፉ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን መንግስትና የገዢውን የፊውዳል ሥርዓት ለማንበርከክና ደርግ በሥልጣን ተፈናጦ ለመቀመጥ እንዲያስችለው እርምጃዎች በወሰደ ቁጥር ያጋጠሙትን ተቃውሞዎች፣ የብሔራዊ ዘመቻንና የሶማሌን ወራሪ ጦር ለመመከትና ወደመጣበት ለመመለስ የተደረገውን ርብርቦሽና በተለይ አኩሪ የሆነውን የታጠቅ ጦር ሠፈር ግንባታና አስተዋጽኦ፣ የገጠርና የከተማ ቤት አዋጆችን ለማውጣትና ለማሰፈጸም የተደረጉ ጥረቶችንና ቅዋሜዎችን፤ የፖለቲካ ቅራኔዎችን ለመግታት፣ ለመገደብ፣ ለማምከንና ብሎም የኮለኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን አምባ ገነንነት ለማረጋገጥ የተደረጉ ፍልሚያዎችን በሰፊው ተንትኗል።

Blue Party’s executives and female members are being accused of freedom of expression!


March 14, 2014
BlueParty Ethiopia
Early in the morning many gathered at the compound of the court house. The appearance was expected to be held at 10:00AM yet only the men arrived. It took the police about an hour after to bring the girls. Most were worried. Then we heard they were being forced to change their shirts that they put on. But they refused to change. After some quarrel at the police station finally they arrived at the court house at 11:08AM.
Blue Party’s executives and female members are being accused
The court house was full of people, some even stood and it was quite humid. After the judge took his place the ones stood were much in number than those who sat. The attorney of the suspected and The Inspector how is handling the case stood by the sides; amid was Blue Party’s young members and leaders of high position.
The case was of course presented 5 days ago and ended with denying a bail for the young activists and members of the party because they were believed to terrorize and as well suspected of disturbance on Women’s Great Run which ended way peacefully.

Wednesday, March 12, 2014


March 11, 2014
ቹቸቤ
የሰማያዊ ፓርቲ ቢጫ ለባሽ ወጣት ሴቶች መታገታቸውን ሰምተን ነበር። አንጋፋው ክስ ደግሞ እናትና አባታቸውን ጮክ ብለው መጥራታቸው መሆኑ ሲነገረን የጥፋታቸው ልክ ታሰበን። የትግራይ ናፃ አውጪዎችና ለነርሱ ለመታዘዝ ፈቃዳቸውን ያሳዩ ገባሪዎች በሙሉ ለተልዕኮ ትምህርት የማይመቹትን እነ ባዮሎጂንና ኬሚስትሪን ዞር አላሉባትም። በርካቶቹ የራሳቸውን ስም ከረሱ የቆዩ ስለሆኑ ዘር በጅምላው እንጂ ቤተሰብ በነጠላው አይገባቸውም። እናም እነዚህ ወጣቶች የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆች ነን ማለታቸው አሸበራቸው።
Arrested Semayawi party members and supporters
ትንሽ እወቀት ያለን እኛ ግን በመጀመርያ ሴቶች ወላጅም አዋላጅም መሆናቸውን እናውቃለንና የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆች ነን ቢሉ አይደንቀንም። እንዲያውም “ጎሸ ሰው ጫካ በቀል አጉራ ዘለል ሲሆን ነው እንጂ የመጣበትን ሲያውቅ ጥሩ ነው።” ብለን ያደነቅን እናቅፋለን የወደድን ለጋብቻ እንጠይቃለን። ወጉ እንደዚህ ነዋ! በጋብቻ ተደራጅቶ የሚኒሊክና የጣይቱን ስም ማቆየት ስለምን ያስፈራል? ዘር መተካት ደግ ነው እንላለን። እንዴ ፌዴራሎች ጠለፋ ይሆን እንዴ የፈፀሙት?
ቢሆንም ልካቸውን ያውቁታልና በሚኒሊክና ጣይቱ በሚሸበሩትም አንፈርድም። ግንቦት ሃያ የተወለዱት ራሳቸውን የፋብሪካ ውጤት አድርገው ስለሚቆጥሩ ተጋዳላይ ድርጅት እንጂ እናትና አባት እንዴት ሊኖረው ይችላል ብለው የመቆጣት መብታቸውንና የማስፈራራት አቅማቸውን ተጠቅመዋል። እናም ድንጋይ ሰባሪ ቅሎቹ ወይም ባለጊዜዎቹ እነዚህን የሚያማምሩ የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችን ተመሳስለው የገቡ ጠጉረ ልውጦች ብለዋቸዋል።

የአባ መላ (ብርሃኑ ዳምጤ) መገለባበጥና ኢሳት


March 11, 2014
እንደልቡ/ዳግም (ከቫንኮቨር፣ ካናዳ)
አባ መላ ማን ነው?
በቅጽል ስሙ “አባ መላ” በእውነተኛ ስሙ ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ ተብሎ ይጠራል፣ በ60ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ አዛውንት ነው (ምንም እንኳ ስራው እንደ እድሜው ባይሆንም)። ፓልቶክ የሚባለውን የማህበራዊ መገናኛ መድረክ በመጠቀም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዲስኩር በማሰማት ይታወቃል። በወጣትነቱ ኢህአፓ ውስጥ ነበር የሚባለው ብርሃኑ ዳምጤ ወዲያውም የኢህአፓን መዳከም አይቶ ወደ ደርግ ቡድን መቀላቀሉን የሚያውቁት ይናገራሉ። በወቅቱ አብረውት በኢህአፓ ውስጥ ይሳተፉ የነበሩ ወጣቶችን ለደርግ በእጅ መንሻ መልክ አሳልፎ ሳይሰጥ እንዳልቀረ በደርግ ካድሬነት ቆይታው የሚያውቁት ይጠረጥራሉ አንዳንዶች ደግሞ አፋቸውን ሞልተው ይናገሩታል።
Aba Mela low rank Ethiopian government cadre
ብርሃኑ ዳምጤ ከደርግ መውደቅ በኋላ በስደቱ ዓለም (ዳያስፖራ) ፖለቲካ መድረክ ብቅ ያለው በምርጫ 97 ወቅት የዝነኛውን ቅንጅት ማልያ ለብሶ ነበር። ይሁንና በስልጣን ላይ ያለው የህወሃት/ወያኔ መንግስት ምርጫውን አጭበርብሮ፣ የምርጫውን መጭበርበር የተቃወሙትን በገፍ በአደባባይ በጥይት ደብድቦ፣ ህዝቡ የመረጣቸውን የቅንጅት አመራሮች፣ ጋዜጠኞችና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ጨመሮ ከ50 ሺህ በላይ ባብዛኛው ወጣቶችን አስሮና በየጦር ካምፖቹ አጉሮ በአምባገነንነቱ ለመቀጠል ሲወስን ብርሃኑ ዳምጤም ባፋጣኝ የቅንጅትን ማልያ አውልቆ የህወሃት/ኢህአዴግን ማልያ ለብሶ ቁጭ አለ።
ሰሞኑን ደግሞ ብርሃኑ ዳምጤ አስደናቂ መገለባበጥን ፈጽሞ የህዝብን አይን አስበልጥጧል። እነዚህ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) ሰሞኑን የሚፈጽማቸው መገለባበጦች በ1960ዎቹ እና 70ዎቹ ከነበሩት የመገለባበጥ ትሪኢቶቹ ለየት የሚያደርጋቸው ነገር ቢኖር አሁን መገለባበጡን የሚፈጽመው በቀጥታ ስርጭት ወቅት (በፓልቶክ) መሆኑና ጉዳዮን በመሪ ዜና መልክ የሚዘግብለት የቴሌቪዥን ጣብያ “ኢሳትን” ማግኘቱ ነው።
ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራቶች በፊት ነበር የተሰለፈበት የህወሃት/ኢህአዴግ ጎራ በተለይም ከወያኔው ቁንጮ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ እየተዳከመ መምጣትን አይቶና ገምቶ ወያኔዎችን “አፍንጫችሁን ላሱ፣ እኔ ከአሁን ብኋላ የድሮው አባ መላ አይደለሁም፣ እንዲያውም ጉዳችሁን አዝረጠርጣለሁ…” በማለት ፉከራ ቢጤ አሰምቶ የዲሞክራሲና የነጻነት ታጋዮችን ጎራ መቀላቀሉን ያበሰረው።

Monday, March 10, 2014

የሴት ነገር ሰማያዊ በቢጫ (ከቹቹቤ)



Ethiopian women protested in Addis Ababa
በተለምዶ የሴት ነገር ስንል የማሳነስ የማቀጨጭ ነው። የሴት ነገር ግን ሁሌም ቢሆን ከዚህ በላይ እንደሆነ ሁላችንም እናውቃለን። የሴትን ነገር የሚያሳንሱ ቢኖሩ ጉልበት አምላኪዎች ብቻ ናቸው። አርግዛ አምጣና ወልዳ የምታሳድግን ሴት እንደ ቅርንጫፍ ከጎድን አጥንት ተሰራች የሚለው አሳናሽ አገላለጽም የሃይማኖት ድጋፍ ይዞ ስለተነሳ ሴቶች ራሳቸው ያነሱ ሆነው እስከሚሰማቸው ድረስ ተጽዕኖ አሳዳሪ መሆኑ እውነት ነው። ዘፍጥረት ወንዴና ሴቴ ሆነው የተፈጠሩትን ሌሎች ፍጡራን (እንስሳውን እጽዋቱን) ሁሉ እግዜር እንዴት እንደፈጠራቸው መናገሩን አላውቅም።  የኔዋ እናት ግን በምንም መልኩ ከኔው አባት አንሳ የጎድን ፍልቃቂው ልትሆን አይቻላትም። እንዴት ተደርጎ! እኔም በማህጸን ውስጥ ሞተር ሲገጠምልኝ፣ እግርና እጅ ሲሰራልኝ አፍንጫ ጆሮና አይኔ ዲዛይን ሲደረግ ስለቆየሁ እርሷ የኔ ፈጣሪ ናት ብዬ ነው እምዬ ስላት ደስ የምሰኘው። እርግጥ ነው የተወሰነ ጥሬ ሃብት ከአባቴ ወስዳለች። በዚያው አይን የኔ የምትሆነው ሴቲቱ ከጎድኔ አንዱ ተቀንሶ እንደተሰራች መቀበል ያዳግተኛል። በእንስሳቱ አለም የሴቶች ሚና እጅግ በጣም ጉልህ መሆኑን ለተመለከተ የሰው ፍጡር ሲሆኑ ሊያሳንስበት የሚችልበት ምንም ምክንያት የለውም። በተለይ በማህበራዊ እንስሳትም ሆነ ነብሳት ውስጥ ሴቲቱ አልፋና ኦሜጋ ናት። ቢሆንም…..ቢሆንም አውቄ በድፍረት ሳላውቅ በስህተት ላልኩት ንስሃ ልግባና ሰማያዊ በቢጫ እንዴት ደስ እንዳሰኘኝ ልናገር።

Sunday, March 2, 2014

ዕርቅና ሰላም፤ የሕይወት ቅመም (ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ)


March 2, 2014
ከፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ
አንድ ጥናት ሳነብ፥ ምናልባት እናንተም አንብባችሁት ይሆናል፥ የተፈጥሮ ሀብት ባላት ሀገር ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ከተራቡ፥  የማሰብ ችሎታቸው ዝቅተኛ ቢሆን ነው ሲል አገኘሁት። “ጥልቀት የሌለው ረጋ-ሠራሽ ጥናት ነው” ብዬ ጣልኩት። የኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብት ባለጠጋ መሆኗን እርግጥ ባለሞያዎች የመሰከሩት ነው። ማዳበሪያ የማያስፈልገው መሬት ታርሶ አያልቅም። የወንዞቿ ውሀ ለጎረቤት አገሮች ሳይቀር ይተርፋል። ይኸንን እውነታ በቀጥታ ከተመራማሪዎቹ  አፍ ለመስማት የፈለገ ፕሮፌሰር ስዩም ገላየን ማዳመጥ ይችላል
Prof Getachew Haile Ethiopia
እንዲህ ከሆነ፥ ትኩረቱ በኢትዮጵያውያን የማሰብ ችሎታ ላይ ሊሆን ነው። እውነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ተመጽዋች ሆኖ የቀረው የማሰብ ችሎታው ዝቅተኛ ሆኖ ነው? አይመስለኝም።  ሰውየው ጥናቱን ማስተካከል አለበት። አለዚያ፥ ከዚያ ቀጥሎ፥ “አንድ ሰው እሱቁ ውስጥ ከመስተዋቱ በስተኋላ ድፎ ዳቦ እያየ ከተራበ የአስተሳሰብ ችሎታው ዝቅተኛ ቢሆን ነው” ሊለን ነው። ምንም ከፍተኛ የማሰብ ችሎታ ቢኖረው፥ ዳቦውን እንደማያገኘው ለማንም ግልጽ ነው።
እርግጥ ነው፥ በአስተሳሰብ ደከም የሚል ሰው ሊጎዳ ይችላል። ሌላው ቢቀር፥ የብልሁ ጓደኛውን ያህል አይደላውም።  ግን በከፍተኛ ደረጃ የማሰብ ችሎታ ያለው ሰውም ሊቸገር ይችላል።  ስንቶች ናቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በችግር የሚኖሩ፥ መውጫ ቢያገኙ ግን ለሌላው ሳይቀር የሚተርፉ? በአፍሪካ፥ በአውሮፓ፥ በአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ በማስተማርና በምርምር ላይ ያሉ ኢትዮጵያውያን ቊጥር ቀላል አይደለም። በንግዱ ዓለምም ቢሆን፥ “የሺ ብር ጌቶችን” ጓዳ ይቊጠራቸው።
የለም፥ የተፈጥሮ ሀብት ባለጠጋ የሆነች ኢትዮጵያ ብልሁ ሕዝቧ ለምን እንደሚራብ የተከበረ ጥናት መደረግ አለበት። ዋና ዋናዎቹን ምክንያቶች ፕሮፌሰር ስዩም ገላየ ደርድሯቸዋል። አንዱ፥ የመሬት ይዞታ መበላሸት ነው ይለናል። “የመሬት ላራሹ” ጩኸት ውጤቱ “መሬት ለነጋሹ” ሆኗል፤ ለገበሬው የታሰበውን መሬት ወያኔ ወሰደው። የዱሮ ንጉሣዊ ገዢዎቿ ቤተ ሰቦች ስለነበሩ በቊጥራቸው ማነስ ምክንያት እነሱን በማር ግብር ለማጥገብና በሰላም ለመኖር ቀላል ነበረ። የዛሬዎቹ ገዢዎች ብሔረ ሰቦች ስለሆኑ እነሱን ሁሉ በሚሊዮን ዶላር ማጥገብ መራቆትን አስከትሏል። ሌላው፥ አገሪቱ በክልል መከፋፈል ነው። ማንም ሰው በገዛ ሀገሩ ከመሰለው ክፍለ ሀገር ሄዶ በሰፊው ማረስ አይችልም። ዛሬ ኢትዮጵያ ለአንድ ኢትዮጵያዊ ሙሉ በሙሉ አገሩ አይደለችም። ኢትዮጵያ ለልጆቿ እናትነቷ በሙሉ ሰውነቷ እንዳይሆን ተከልክላለች።