Monday, May 19, 2014

ከዞን-9 ታሣሪዎች ስድስቱ ፍርድ ቤት ቀረቡ

ፖሊስ በሽብር አድራጎት እጠረጥራቸዋለሁ ብሏል፤ ፍርድ ቤት የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የዞን-9 ብሎገሮች በእጅ ብረት ታስረው ወደ ችሎት ሲወሰዱ
የፊደል ቁመት 
መለስካቸው አምሃ
 —   
የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/የታሠሩት ብሎገሮችና ጋዜጠኞች /የፎቶ ምንጭ - ኢንተርኔት/

ላለፉት 23 ቀናት ክሥ ሳይመሠረትባቸው ታስረው ከሚገኙት ዘጠኝ የዞን ዘጠኝ የኢንተርኔት ሚድያ ፀሐፊዎች የሆኑ ጋዜጠኞችና አምደኞች ስድስቱ ዛሬ፤ ቅዳሜ፣ ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ስምንተኛ ወንጀል ችሎት የጋዜጠኞቹንና የአምደኞቹን ጉዳይ ያየው በዝግ ሲሆን የቀረቡት ጋዜጠኞቹ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋዓለም ወልደየስ እና ኤዶም ካሣዬ እንዲሁም ሌሎች ሦስት አምደኞች መሆናቸው ታውቋል፡፡
  
የዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡየዞን-9 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች አራዳ ፍርድ ቤት ቀረቡ
ዛሬ ችሎት ያልቀረቡት አምደኞች መቼ እንደሚቀርቡ ለጊዜው በትክክል ባይታወቅም ሰሞኑን ይቀርባሉ የሚል ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡

Thursday, May 15, 2014

እምዬ ምኒልክ ሲመጥቅ፣ ወያኔ ሲወድቅ


May 15, 2014
ከሮበሌ አባቢያ፤ 14/5/2014
ቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ
ወያኔ በ1983 አዲስ አበባ ሲገባ እግረ መንገዱን የገበሬውን ልጆች፣ ጋዳፊና የአረብ ሀገር ከበርቴዎች ባስታጠቁት ዘመናዊ ታንክና መሣሪያዎች፣ እያጨደ በሬሳቸውና በደማቸው ላይ እየተረማመደ እንደነበር መሪር የቅርብ ትዝታ ነው። በቅጥረኛው አምባገነን መለስ ዜናዊ ይመራ የነበረው ጎጠኛው የወያኔ መንግሥት፣ የኢጣልያ ፋሺስት ያወጣውን በተለይ በአማራና በኦሮሞ ላይ ያነጣጠረውን የከፋፈለህ ግዛው ፖሊሲ ኮርጆ በመከተል፣ የአፄ ምኒልክ ሐውልት እንዲፈርስ ለማደረግ ሕዘቡን አነሳስቶ እንደነበር ይታወቃል።ሆኖም ሙከራው ወያኔ አስቦት በነበረበት ወቅት ባይሳካም፣ ሐውልቱን የማንሳት ሃሳብ አሁንም አለ። ስለዚህ ሕወሐት የሚመራው በውስጡ በሚስጥር በተሰገሰጉ ባንዳዎች እንደሆነ እያደር ሊታወቅ ስለቻለ የእምዬ ምኒልክ ወደጆች መዘናጋት የለባቸውም።
Ethiopian king Atse Menelik
ሐውልቱና ከኢጣልያን ጋር የተደረጉት ሁለት ከባድ ጦርነቶች
እምዬ ምኒልክ፣ እስከ አፍንጫው ድረስ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ በገፍ ታጥቆ ኢትዮጵያን ሊወር የመጣውን ጦር፣ አድዋ ላይ ገጥመው ወራሪውን ድባቅ መትተው አንፀባራቂ ድል ሲጎናፀፉ፣ ከሰሜን ሸዋ አብሮአቸው የዘመተው ስምንት ሺህ (8000) ፈረሰኛ የኦሮሞ ሚሊሽያ ሠራዊት በጦርነቱ ለተገኘው ድል ወሳኝ አስተዋፅዖ አድርጎ እንደነበረ በታሪክ የተመዘገበ የጀግንነት ሐቅ ነው። የአድዋው ድል የአውሮፓን ሀያላን መንግሥታትን አስደንግጦ ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሉአላዊ ነፃ ሀገር እንዲያውቋት አስገድዷቸዋል። ይህ ታላቅ የጥቁር ሕዝብ ድል በዓለማችን ላይ ለሚገኙት ጭቁን ጥቁሮች ሁሉ ሕያው ተስፋ ሰጥቷል።
በሽንፈቷ ሀፍረት የተከናነበችው ኢጣልያ፣ 40 ዓመት ሙሉ በሚስጢር ስትዘጋጅ ቆይታ፦ ሀ) በሚሊሽያዎቻችን ላይ ከሰማይ በአውሮፕላን የቦምብ ናዳ በማዝነብና በዓለም ሕግ የተከለከለውን መርዝ በመርጨት፤ ለ) በምድር በታንክና በመትረየስ የታገዘ መጠነ ሠፊ የሰለጠነ እግረኛ ጦር በማዝመት፤ ሐ) ሕዝቡን በጎሳ ከፋፍላ እርስ በርሱ በማጫረስ፤ መ) አማሮችና ኦሮሞዎች የሥልጣኔ ተፃራሪዎች ስለሆኑ ሌሎች ጎሳዎች በጠላትነት እንዲፈርጇቸው በመስበክ፣ አዲስ አበባን (ሸገርን) እንደ አውሮፓ ዘመን አቆጣጠር በ1936 ዓ.ም ለመቆጣጠር ችላለች። ዋቢ፦ Habešská Odyssea (YeHabesha Jebdu) የሃበሻ ጀብዱ by Adolf Parlesak Translated by Techane Jobre Mekonnen
የፋሺስትን ወረራ ያልተቀበሉት የኢትዮጵያ አርበኞች (በአዲስ አባባና በአካባቢው የሚገኙትን ኦሮሞዎችን ጨምሮ)፣ አራዳ ጊዮርጊስ በዳግማዊ ምኒልክ ሐውልት ዙሪያ ማታ ማታ እየተሰበሰቡ (ሬዲዮ አድማጭ መስለው) ይመካከሩ ነበር። ግራዚያኒ ይህን ሲሰማ ሐውልቱ እንዲነሳና በምሥጢር እንዲቀበር አዘዘ፤ በትእዛዙም መሠረት ሐውልቱ ተነስቶ ሌላ ጋ ተቀበረ። ፋሽስት ኢጣልያ ተሸንፎ ከሀገራችን ሲባረር፣ ሐውልቱ ከተቀበረበት ቦታ ተመልሶ እንደገና በቀድሞ ቦታው ላይ ሊተከል ቻለ።
ጠላት ተገዶ ያከበራቸውን እምዬ ምኒልክን ማክበር የምንኮራበት መብታችን ነው። እምዬ ምኒልክ ሲልቅ፣ የባንዳዎች ውላጅ ወያኔ ሲበሽቅ ሁሌ እደሰታለሁ። ምኒልክ አንድ ያደረጋትን ኢትዮጵያን ወያኔ ሲበታትናት አበክረን መቃወም የውዴታ ግዴታችን ነው። በዚህ ጉዳይ ለሚቃወሙን ተቺዎች መልሳችን ይሄው ነው።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር
አፄ ምኒልክ ከአንኮበር ወደ ሸገር ሲመጡ ያጋጠማቸው ተፋላሚ ቱፋ ሙና የተባለ ሐይለኛ የኦሮሞ ገዢ ነበር። አፄው ብልሀተኛ ስለነበሩ አማላጅ ልከው ታረቁና ቱፋ ሙናን ክርስትና አንስተው አበልጅ ሆኑ። የቱፋ ሙና ሰፊ ዘሮች እነ አቶ ብሩ ጎሮንቶ ገፈርሳ ግድብ አካባቢ በስተ ምዕራብ-ደቡብ አንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ይኖሩ ነበር። አቶ ብሩን ባጋጣሚ ሱሉልታ አግኝቻቸው ከተዋወቅን በሗላ፣ ከባለቤቴ ጋር ገፈርሳ ድረስ እየሄድን እንጠይቃቸው ነበር። አቶ ብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ፣ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ በተገኘበት በታላቅ ሥነሥርዓት ገፈርሳ በምትገኘው ቅድስት ማርያም ቤ/ክ በተፈፀመው ቀብራቸውም ላይ ተገኝቻለሁ።
ምኒልክ ከአንኮበር እስከ ሸገር (አዲሰ አበባ) የመጡት በኦሮሞ ባላባቶች የሚታዳደሩትን ግዛቶች አቋርጠው ነው። ቱፋ ሙና ብቻ ነው በነውጥ የተፋለማቸውና ውጊያው በእርቅ የቆመው። በነገራችን ላይ፣ የ1966ቱ አብዮት ሲፈነዳ እኔ አሰከማቀው ድረስ በሸዋ ውስጥ ሰፍኖ የቆየው ባላባታዊ ሥርዓት አራማጆች በአብዛኛው አለጥርጥር የኦሮሞ ተወላጆች ነበሩ።
የተወለድኩት አዲሰ አበባ ቀጨኔ ጋላ ሰፈር በሚባላው መንደር ውስጥ ነው። የከተማውን ዙሪያ ደህና አድርጌ አውቃለሁ። ሸዋ ውስጥ በልጅነቴ በእግሬና በፈረስ ከዚያም ስጎረምስ በመኪና በብዙ አቅጣጫዎች ተዘዋውሪያለሁ። ለምሳሌ፣ ከአዲስ አበባ ተነስተን እስከ 130 ኪሎሜትር ርቀት ዙሪያውን በወፍ በረር ብንቃኝ፣ የክልሉን ባላባትነት የአንበሳውን ድርሻ የኦሮሞ ተወላጆች ይዘውት እንደነበር አያከራክርም ለማለት ይቻላል። አፄ ምኒልክ የመሬት ግብር አስከፈሉ እንጂ የባላባቶችን የመሬት ይዞታ አለምክንያት አልነኩም። ዘውዱንም መሬቱንም እኔ ይዤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ምን ሊቀረው ነው ብለው የመሬት ባለቤትነት በግል የእያንዳንዱ ዜጋ ይዞታ መሆን እንዳለበት በችሎት ላይ ስለመፍረዳቸው በአድናቆት ይነገርላቸዋል።

Monday, May 5, 2014

TPLF/EPRDF’s Divisive and Polarizing Political Master Plan is the Problem: Addis Ababa Master Plan is simply the Symptom


May 5, 2014
by Alem Mamo
The suffocatingly oppressive political rule of TPLF/EPRDF has continued to terrorize the people of Ethiopia, denying them their basic human rights to live in peace, dignity, and inclusive harmony. Since coming to power in 1991, the TPLF-led regime has implemented a deliberate system of permanent polarization and suspicion between and among communities. Obviously, the objective of this policy of permanent polarization and compartmentalized order is to weaken the ability of the Ethiopian people to resist and defeat this brutal totalitarian regime.
Addis Ababa Master Plan
The genesis and history of TPLF/EPRDF is deeply tied with its addiction to violence, murder, torture, and mass terrorization. The events of the last two weeks in Addis Ababa, Ambo, and other parts of the country are a clear testament of TPLF/EPRDF’s violent nature and it’s disregard for the sanctity and dignity of human life. First, there was the arrest of nine Zone 9 bloggers for no other reason than reporting and speaking truth to power. These young members of Zone 9 are representatives of their generation, committed to taking their rightful place in history. They knew all too well that the regime’s intolerance and even disdain for press freedom could make them a prime target. However, these young budding journalists/bloggers continued to inform the public and expose the crimes of the regime to the world, even if it meant going to jail and facing all physical and psychological suffering that comes with imprisonment. Their arrest has reaffirmed the fact of the TPLF/EPRDF regime’s unflinching commitment to keeping the people of Ethiopia under its clenched fist, and their fear of what Zone 9 bloggers/journalists are doing to report and resist. As the bloggers/journalists have articulated, there are two types of prisons in Ethiopia: the notorious Makalawi (which is divided into 8 zones) and prison dungeons spread all across the county; and the open-air prison which is the entire country (and where the name Zone 9 comes from). The bravery of these young bloggers/journalists is a profound lesson to all who fight for democracy, freedom, and justice, and their message is clear – freedom is not free!